Tuesday, December 18, 2012

አሸናፊ አባባሎች



በፉከራ በቀረርቶ ወይም በስራ አልባ ህልም ተፈጥሮ አትረታም::
የታለመ ተግባር ግን የማይቁዋረጥ ስራ ግን ያንበረክካታል::
አሸናፊ መሆን የሚሹ ኢላማቸውን ይሰሩታል ይኖሩታል!!

በማንኛዉም አንድ ጉዳይ ላይ ከሁሉም ጋር ለመግባባት የሚሹ ሰዎች
እብዶች ናቸው
በሁሉም ነገር ከሁሉም የሚለይ እና በሁሉም ነገር ከሌሎች ጋር የሚመስል
ሲጀመር እብድ ነውና
ብልሆች ህጋዊ በሆነና ባመኑበት ጉዳይ ይሰሩበታል
የሚስማሙትንም የማይስማሙትንም አክብረው!!!

መሆን የምትፈልገውን አትቅጠር ዛሬ ላይ ሁነው አድርገው
አለም ለይሉኝታህ ግድ የላትም
ተግባርህን ግን ትከፍለዋለች
ቁምነገሩ ክፍያህ ትልቅና በጎ እንዲሆን በአግባቡ መተለም 
ብቻ ነው!!!

ዛሬን እንዳመነው እንኑረው ደስታ የወደዱትን መኖር መቻል ነውና
ወሬውን ለባዮቹ ተወው ወሬያቸው እምነታቸው እንጂ እምነትህ አደለምና
ያንተ የሆነው እምነትህና ያንኑ የምትኖርበት ግዜ ዛሬ እና አሁን ብቻ
ናቸው!!! በቃ ኑረው ሁነው!!

አገርም ዛሬ በታመነው ዛሬ የሚሰራባት የኛ ስብስብ እንጂ
የንትርክ ቅርጫ የጭቅጭቅ መድረክ አደለችም
ዛሬ ስንሰራ የምታድግ
ስንነታረክ ደግሞ
እምትማስን ናት 
የሚወዱዋት ዛሬን ይኖሩታል!!!

Monday, December 17, 2012

Implications of World Bank Economic Report for Ethiopia


                                                                                       Zeryihun Kassa
The World Bank Report illuminates the outstanding performance of Ethiopian economy over the last nine years since 2004. It shows Ethiopia has a lion economy in Africa propelling at a pace the East Asian tigers have done.

Nine Years of Epic Economic Feat
The World Bank Report says “Ethiopia has experienced strong and generally broad-based real economic growth of around 10.6% on average since 2004 - 2011.”
Thursday (13 October 2012) saw the launching of the World Bank Report on Ethiopia’s Economy at the Sheraton Addis.
Most often some try and contest Ethiopia’s annual growth report assuming the government may cook data to portray exaggerated picture of the reality. Yet, no credible international institution has denied the fast powering economy of the country.

Here is another testimony by the World Bank that illuminates the strong showing of the state of the economy for a little less than a decade: “The growth over the last nine years,” the report read, “was far beyond the growth rates recorded in aggregate terms for Sub-Saharan Africa, which is 5.2% - less than half of Ethiopia’s average real GDP growth rate during that period.” It seems currently Ethiopia is the increasingly growing, non-oil tiger economy in Africa.

The report indicates Ethiopia’s growth appears to have been inspired by the East Asian experiences namely those of countries like China, Korea and Taiwan. It is reported to have been induced by a mix of factors: agricultural modernization, the development of the export sectors, strong global commodity demand, and government-led development investments, among others.
Growth is estimated to likely stay around that remarkable margin up until 2016.

Poverty Reduced by 9.1%
The growth over the 5 years spanning from 2004/5 to 2009/10 has lifted around 2.5 million citizens out of poverty, thereby bringing down people under the poverty line from 38.7% to 29.6%, which is a 9.1% decrease.
The report further estimates, given inflation kept tamed, Ethiopia is highly likely to make its target of the Growth and Transformation Plan (GTP) reducing the poverty by another 7.4%.
The national poverty line here is less than US$0.6 per day. The report suggests it is so important for Ethiopia to take the inflation down to maintain the hard-won reduction in poverty.

Export on the Rise
The World Bank Report appreciates the country’s strategy of increasing exports to facilitate growth as it is the development pattern of recently successful countries particularly in East Asia. Ethiopia’s export products showed growth of 14.8% in 2011/12.
Boosting the export sector is appropriate, the report noted, given the current limited size of the country’s domestic market.  Considering the composition of the export by commodity, still coffee continues to be the largest export while Gold closely follows behind. Despite recent decline in volume of coffee export, trends suggest it will rebound. Ethiopia is also diversifying its export with rising sale of oil seeds, flowers, live animals, fruits and vegetables.
The growth in export of goods, the report says, is to a good extent driven by volume growth across a variety of product groups which is a result of recent efforts to increase and diversify the export base.
However, the increase in annual import goods by 33.5% in 2011/12 alone indicates the overall import/export development resulted in a significantly bigger trade deficit, which stood at 7.9 billion US Dollars in 2010/11.
Inflation Still a Threat
Though headline inflation rate in October 2012 was 15.8%, it was over 33% in 2011. Currently inflation is declining slowly.
The reduction in inflation, according to the World Bank Report, is down to the tightening fiscal stance and monetary base growth induced by the government of Ethiopia.
The hope is, in spite of its persistence, inflation will remain in a descending trend.    

Ethiopia’s Economic Growth vis-à-vis China, South Korea
The World Bank Report shows interesting comparisons of Ethiopian development experience to China and Korea which depicts Ethiopia is well on track. Yet, the country has to significantly boost its domestic savings and exports performance while keeping inflation down to single digit.
Although there are few peculiarities between them, by and large, Ethiopian economy is following the two fast tracking economies-the Republic of China and South Korea.
Based on policies observed in China in the 1990s, the comparison depicts, there are a series of “quick-wins” that could be used to increase the potential for FDI inflows into Ethiopia.
According to the Report, Ethiopia’s fiscal performance appears to be adequate given the current state of the economy and financing requirements for development.


 Opportunities for more growth
The current state of the economy is a plus for investment in Ethiopia. Besides the strong political stability and investment incentives are luring. Yet still there are rooms for improvement to become a major destination of global investment.
The cheap abundant labour, the size of the population and cheap electric power are some of the appeals to FDI and massive local investment, given the government sorts out some logistic doldrums that somehow hampers the progress.
The impressive annual economic growth that endures for nearly a decade is another incentive to bring in much-needed FDI in a way it further fuels the already fast-paced economic development.
No doubt, I assume, if the country sustains this growth momentum for a couple of decades, Ethiopia will become a shining gem in the horn of Africa.

Challenges of the Economy
Among the challenges the World Bank Report surfaced, one is the poor saving rate of the country.
The Report says “Even though Ethiopia achieved high income growth it is striking that the country has not reached the subsistence level beyond which people start to save in earnest.” Therefore, it is essential to considerably increase the domestic saving.

The other challenge is the logistics problems that most often complicate things for investors. Indeed, the World Bank Report and investors attending the launching of the report admired the incentives Ethiopia has offered. Yet they see a number of gaps specially related with customs regulations and other logistic matters.
One such example is the cost of shipping from china to Djibouti and the cost of shipping from Djibouti to Addis Ababa is the same which is odd given the big disparity in distance. Participating investors asked the government to fill in the gaps so that the investment climate for both domestic and foreign companies will be much smoother. 

Saturday, December 15, 2012

The fool, the evil, the critics and the wise




                                                                      Zeryihun Kassa 
For me those who wish everything to be clean just will never get anything done. Either they don't try or if they do then, they will quit it in the middle stating it will hurt this and that people or environment.

The evil want do for themselves even if it means to hurt someone else, even others' lives. Their compass doesn't see anything other than themselves. They see other people like any expense. This kind of men ruin a nation, community, individuals and institutions.


The critics sitting on the sidelines enjoy telling us this is wrong and barbaric. They only see what is bad. Even if you involve them in a certain project they will make your life miserable telling you the wrongs happening. The worst thing is they never make right the things they see wrong. They enjoy their privilege of putting mud on anyone they assume responsible. Irrelevant they are!



The wise see things going wrong. They know the world just doesn't become pure. Yet with effort they know dominantly things can go the best way possible. Therefore, they try and identify the most essential things which needs shift and work their way through to get those things mended. 



This they do in all their power to make it ok for everybody else, to create a good place to live. They don't expect anyone to do it for them. They know they are prone to mistakes and if anything goes wrong they admit and work to improve and correct. But they don't intentionally hurt the interest of others.



They don't see the world as all black or white. They try and see as it is and do their best to shape it the way most agrees it to be. Because they believe in their power they also believe in the power of everybody else, therefore work to form a very strong team to get their mission done.



I am proud of wise people and want to follow their suit. I think the rest either should get changed to be of help or left aside as they don't matter despite being a noise on the sidelines.



See you with another piece.

Wednesday, December 12, 2012

አቤቱ የሚሰሩና የሚለውጡ ጀግኖች ስጠን


                                                       በዘርይሁን ካሳ
ቴዎድሮስ ተወደደም ተጠላም ያመነበትን አሳምኖ ቡድን አደራጅቶ የመሰለውን ታሪክ ሰርቶ አልፍዋል የሗንስም እንዲሁ::

ምንይልክም በግዜው እምነቱን ሰብኮ ጦሩን አደራጅቶ ያመነበትን ሰርቶ አገርና ታሪክ ትቶልን ተሰናብቱዋል:: ትልቁ ነገር ዳር ቆሞ ሲቆዝም ወይም ሲቦጭቅ አልነበረም እምነቱን ሌሎችን አሳምኖ ጭምር ኖሮታል:: 
አንዱ ደማቅ ገድሉ የጥቁር ነጻነት ምልክት የሆነበት አድዋ ነው እማይወደዱ ታሪኮችም ይኖሩታል በቁምነገሩ ግን ዘመኑን እምነቱን ኖሮበታል::
ዳር ቆሞ ሲያላዝን በጁ የያዘውን አላባከነም አለያም ደግሞ ሰዎች የያዙትን ሲያጠቁር ግዜው አልረፈደበትም::

ሀይለስላሴም ታሪክ ያለውን ሊል ይችላል ይሉኝን ፈርተው ፍላጎታቸውን እና እምነታቸውን ሳይኖሩ የቀሩ አልነበረም:: የወደደም ወደደ የጠላም ጠላ አቁዋማቸው አገር መርቱዋል ምንም ይስሩ ትክክልም ይሁኑ አይሁኑ ሰርተዉታል::
የሳቸው አመራር ያላማራቸው ተማሪዎች ደግሞ ንጉስ ሆይ መንገዱ ለህዝባችን አይጠቅምም ብለው ታግለዋቸዋል::
ወታደሮቹም ያግኙትን አጋጣሚ ለበጎም ይሁን ለመጥፎ አላባከኑትም እሚያነሳት ያጣችውን የተማሪ አብዮት የፈጠራትን ለውጥ ቀልጠፍ ብለው በመነሳት አገር መርተዋልም ገለዋልም:: ቁምነገሩ ደፈር ብለው ሀላፊነት መውሰዳቸው ነው::

ለውጡ ያላረካው የተወሰነ ተማሪ ትግሉን ከትምህርት ቤት ወደ ደፈጣ ውግያ ቀይሮ ጫካ ገብቶበታል::
ያላሳመነውን ለውጥ በዳር ቁዋሚነት እንደማያሳካው ተገንዝቦ የሚያምንበትን ለውጥ ለማምጣት ህልሙን ትቶ ዲንጋይ ተንተርሶለታል:: መስዋእትነት የሚጥይቀውን ለውጥ በጫጫታ ለመመከት አልሞከረም ትግሉ የሚጠይቀውን ዋጋ ለይቶ ለአመታት ከፍሎታል::

ትግሉ ወጤት ካስገኝም በሁዋላ የድሮዎቹ ተማሪዎች አገር መርተዋል:: እየመሩም ነው:: እምነታቸውን እሚጋራም እማይጋራም አለ:: ያ ለውጥ የለውም:: ቁምነገሩ እምነታቸውን አላማቸውን ከመፈጸም ያልቦዘኑ መሆናቸው ነው::

ቁጥሩ አስማማም አላስማማም አገር እያደገ ነው:: እቺ አገር ግን የትላንቱን ችግር ብትሻገርም ዛሬም ችግሮች አሉባት መቼም ይኖራሉ::  ዳር ቁዋሚ አዝማሪዎች ግን ችግር አይፈቱም:: አገር አይቀይሩም:: ቀይረውም አያቁም::

ዛሬም አገር የምትሻው  ጨለማን የሚረግም ዳር ቁዋሚ አዝማሪ አደለም:: በገባውና ባመነበት ልክ እምነቱን የሚኖር ለለውጥ ዋጋ የሚከፍል እሚችለውን ታክል ደግሞ አስተዋጾ እሚያበረክት ጎበዝ ነው::
በርግጥ ሂትለርም መሪ ነው ማንዴላም ያው መሪ ነው:: ሙሶሊኒም ጋንድሂም ያው ስማቸው መሪ ነው:: በረከታችን ግን የማንዴላንና የጋንድሂን አይነት እንዲሆን ከመተለም እና ቁርጠኛ ከመሆን ጋር ሲሆን የበለጠ ህዝብ ይጠቅማል ቢያንስ ደግሞ አይጎዳም::

ከሁሉም ግን የከፋው ዳር ሆኖ ማጨብጨብ ነው:: ነጋ ጠባ ላይፈይድ ማንቦጫረቅ::

የቅርቡን እንኩዋ አብነት ብንወስድ ሰው እንዲወደውም እንዲጠላውም አደለም የሚውዱትን ያክል  የሚጠሉትም እንዳሉም ያውቃል ግን ለሀገሬ ይበጃል ያለውን  እስከህቅታው ድረስ አንድ ጎበዝ ኖሮታል::

ተወደደም ተጠላም ምጡቅ ስብእናው እና ብቃቱ ግን አነጋጋሪ አደለም መላውን አለምና አፍሪካን በተግባራዊ ፍልስፍናዎቹ ተጽእኖ አሳርፎባቸዋልና::

ቢያንስ ከማላዘን በሁሉም ጉዳይ ላይ ከሁሉም ጋር የሚግባባውን ያልተወለደውንና መቼም የማይወለደውን ጸአዳ መሪ ከመጠበቅ እምነታችንን እና ግቦቻችንን ባመንበት አማራጭና መንገድ እንኑረው::  የዘመኑ ባለምጡቅ ስብእና መለስ ዜናዊ ትቶልን ያለፈው አብነት ይኸው ነው::

መላእክትን አደለም ስህተት ሰርቱዋል ምርጥ ሰው ግን ነው አንጸባራቂ ድሎች ለኛና ለሀገራችን ትቶልን አለፉዋል::

አትፍራ ከፊሉ ያደንቅሀል ከፊሉ ይኮንንሀል እምነትከህን ግን በምልአት ኑረው ትርፉን ታሪክ ይተርከው::
ይቆየን:: 

Tuesday, December 11, 2012

ትዝብቴ



ሁላችንም ችግር አለ ባዮች ነን።

ታክሲ ችግር፣ ቤት ችግር፣ ራስ መቻል ችግር፣ ስራ ችግር፣ ግንኙነታችን ችግር። ችግር ያልሆነ ነገር ያለ አይመስለኝም።በግልባጩ ደግሞ እነ እገሌ ናቸው የሚል ጣት መጠቆም እንጂ ሃላፊነት የሚወስድ የለም።

እና ግራ የሚገባኝ ችግሩን ማን ፈጠረው ሊባል ነው። ይህ እኔን ይመለከተኛል የሚል ሃላፊነት መውሰድ የሚችል ልምድና ስብእና በሌለበት እውን የችግሮቹን መነሾ ፈትሾ መፍትሄ የሚሰጠው ማን ሊሆን ነው።

እቺ ሸሸት ሸሸት እምታዋጣን አይመስለኝም እንዲያውም በሺዎች ለሚቆጠር ታሪካችን ሁነኛ መለያ ልምዳችን ሀላፊነት መውሰድን መጥላታችን ይመስለኛል። ለድህነታችንም ሁነኛው ምክንያት ይህ ይመስለኛል።

እኔን ይመለከተኛል ያልን እንደሆነ ምን እንዳይሆን ነው። ክደን ኖረን አይተነዋል ከዛሬ ጀምረን የለም አልሸሽም ይህ የኔ ጥፋት ነው ማለት ብንጀምርስ። ባላጠፋ እንኩዋ ይህን እኔ ሀላፊነት ወስጄ ልፍታው ማለት እንልመድ። ማንም በጥፋተኝነት አይረገም ግን እሺ ማን ይፍታልን ችግራችንን? አማልክት?! አይመስለኝም::

አለም የተለወጥችው ሀላፊነት መውሰድ በቻሉ አንዶችና ጥቂቶች እንጂ በችግር አለ ባይ ባዶ ጭሆቶች አደለም። ችግሩን የተረዳው ዳዊት መፍትሄውን ካላመጣ ዳዊት አደለም። 

መፍትሄው ችግሩን መተረክ ሳይሆን ችግሩን ፊትለፊት ባመንበት አማራጭ መጋፈጥ ነው። ስትጋፈጥ አትወደድ ይሆናል መፍትሄ ግን ስለመሆንህ ጥርጥር የለውም።

Monday, December 10, 2012

PROBLEM IN ETHIOPIAN POLITICS

                                                   By  Zeryihun Kassa
This is the problem is not here is the solution. The Davids Ethiopia seeking are not those who tell us: this is the problem, he is the problem, they are the problem, it is the problem, these are the problems, it is the problem .... Hey, Stop it. Don't mention it anymore. We are here for the solution. Our life speaks for itself that there is a problem. The pains in our life are proof of the presence of problems.

It feels like the dominant pattern in our political and social life is explaining there is a problem, here is the problem, here comes the problem, I told you this is the problem... then what? That is the problem is not the solution either. 

Stop becoming another problem, telling us what we already know. Please showcase the solutions: you believe will work to solve the existing problems. Come on, bring us one such solutions with doable blueprints and then, the people if convinced, let you have the political leadership to drive the country with the blueprint that gets the vote of the public.

Solution makers are not free of mistakes. Don't tell us they do this and that wrong. If somebody dominantly sails the water with the right map despite the dangers out in the sea, he is doing his job. 

Guys you can no more tell us there is a problem and use it as a proof to your leadership capability. Rather make sure you are the right tool who can deliver the best of the solutions for prioritized problems which need radical and profound shift.

This country can't be fixed with band-aid and aspirin. Emergency treatment is not the solution. We need something that cures the chronic causes of the problems than mechanisms attending acute, painful symptoms. 


It is good to grow and get matured enough to plot and deliver solutions. Poor rhetoric for itself speaks, that you haven't become the solution.

If it is to be of real significance and one who can really contribute for social and economic well being of society, it is good to grow into competence and character that work to produce blueprints to solutions. Besides it is good to grow to become one who is committed enough to get the blueprint done despite whatsoever.

Here is the problem is not here is the solution. Let's leap this nonsense if we really want to help build our beloved country.//

Wednesday, December 5, 2012

የኛ አገር ፖለቲካ


እኔ እንደሚገባኝ ችግሮቻችንን መላእክት አይፈቱልንም፡፡ እኛው ላቁጠን፣ ፈግተን እና ዋተን የምናመጣው እንጂ እነ እገሌ ምነው ይህን አድርገውት ቢሆን ኖሮ በሚል ጠባቂነት አደለም፡፡ በአገራችን ችግር ካለ እኔና አንተም ችግር ከሚፈጥሩቱ ወይም ችግሩን ለመፍታት ከማይሰሩቱ ስለምንሆን ከመጠየቅ አንድንም፡፡ እየሞከርክም ከሆነ ችግሩ እስካልተፈታ ዛሬም ትተቻለህ፡፡ ለለዉጡም በጥረትህ ልክ ከሚመሰገኑት እኩል ትመሰገናለህ፡፡

በርግጥም የምትሳበው ለሀገርህ እንደሚጠቅም የምታምንበትን እንደሆነ እገነዘባለሁ፡፡ ሁሌም ያንተን ሀሳብ የማይጋሩ ግን ደግሞ ለሀገሬ የሚጠቅማት መንገድ ይህ ነው ብለው ያንተን በመሰለ ተቆረቁዋሪነት መንፈስ የሚተጉ ሌሎች እንደሚኖሩ እረዳለሁ፡፡ ዴሞክራሲያዊ ፖለቲካ የብዙሀን ፓርቲ ስብስብ የሚሆነውንም እኮ ለዚህ ነው፡፡

ያም ሆኖ የኛ አገር ፖለቲካ በጡዘት የተወጠረ ይመስላል፡፡ እንዲህ ያለውን ልዩነት እንደመድረኩ ባህሪ ወስዶ ሲያበቃ ባሻገር ያለው ባለ ልዩው አቁዋም ቡድንም ሀገሬን ይጠቅማል ብሎ የሚያምንበትን አቁዋም መያዙን መቀበል ተገቢ ነው፡፡ እነዚህ ሌቦች ሆዳሞች የሚል ቅፅል በመጨመር ራስን ልዩ የሀገር ተቆርቁዋሪ አድርጎ ማቅረብ ስህተት ነው፡፡

ያም ሆኖ ግን የአላማዉን ልዩነት ገምግሞ አይጠቅምም ብለን የምናምነው አቁዋም በህዘቡ ተቀባይነት እንዳያገኝ መስራት ተገቢና ትክክል ነው፡፡ ይህን ብሎ መስራት ግን መሰዳደብና መወራረድ ለመተያየት ሁሉ መጠላላት መድረስ ማለት አደለም፡፡ ፖለቲካችን ይህን የመሰለ ስክነት ይፈልግ ይመስለኛል፡፡

ተቆርቋሪነቱ አበረታች ነው፡፡ የራስን ተቆርቋሪነት ልዩ አድርጎ ማየትና ሌሎችን ማንኩዋሰስ ግን ጎጂ ልምድ ስለመሆኑ አያጠያይቅም፡፡  የራስን እቅድ የተሻለ መሆን ማስረዳትና የህዝብን የላቀ ድጋፍ ለማግኘት መትጋት ይቻላል፡፡ የራስን የመፈጸም አቅምና ልምድ ማጉላትና የህዝብን አመኔታ ለማግኘት መትጋት አግባብነት አለው፡፡

በዚህ ደረጃ መረዳቱ ያለው ሰው ዳር ቆሞ እነገሌ ያደረጉትን እና ያላደረጉትን እየጠቀሰ ማሄስ እንደሚችል እረዳለሁ፡፡ ሆኖም ትችትን እንደሁነኛ ሚና መቁጠር ግን ትንሹ አማራጭ ይመስለኛል፡፡ ይጠቅማል ብለን የምናነውን ጉዳይ በሚመስለን ፓርቲ ተቀላቅለን መትጋትና አስተዋጾ ማበርከት ስንችል ከመአዱ እንዳባረሩት ሁሉ ራቅ ብሎ ማማረር በጎው ሚናችን ነው የሚል የዋህነት የለኝም፡፡ እናስ መቆርቆራችንን በተግባር መግለጽ አንችል ይሆን

ተወዳድሮ ያሸነፈን በአቁዋሙ የተለየን ፓርቲ የምንሻውን እንዲፈጽም መመኘት ሞኝነት ይመስለኛል፡፡ አሸናፊ ፓርቲ የተወዳደረበትን አቁዋሙን ከመፈጸም ወደሁዋላ  አይልም፡፡ ይህ እንደማይበጅ ካመን ያዋጣል የምንለውን አቁዋም ህዝብ እንዲቀበለን በማድረግ ገዢ ፓርቲን መርታትና በእምነትና አቁዋማችን ልክ መምራት እንጂ ዳር ቆሞ ማላዘን ከንቱነት ይመስላል፡፡ ለኔ ዳር ሆኖ ከሚወተውት ገብቶበት ለመስራት ሲሞክር የሚሳሳት ይሻለኛል፡፡ እናስ ትግሉን ብንቀላቀለው፡፡

ወደድንም ጠላንም አሸናፊ ፓርቲ ያመነበትን ይሰራል መሪያችንም ሆኖ ይቆያል፡፡ ሁኔታዉ የማያምር እንደሆነ ካመን የሚያምረንን ለማምጣት እየሰራን ለግዜው የሚመሩንን አክብረን መቀጠል ይኖርብናል፡፡ መቃወማችን እንዳለ ሆኖ የሀገሬ መሪ ነዉ፡ አሸንፎ ነው ቦታዉን የያዘው ብሎ ማመን ይጠይቃል፡፡ ሁሌ እኛ ካላሸነፍን ተጭበርብሩዋል የሚለው ልቅሶ ሰሚ የሚኖረው አይመስለኝም፡፡

ሲደመደም ዳር ቆሞ የመቦጨቅና የመተቸት ማበረታቻ እና ክብር ያለን አይመስለኝም፡፡ ለመፍትሄው ከሚተጉት መሀል መሆን ይመረጣል- በርግጥም እንደምንለው አገራችንን የምንወድ ከሆነ፡፡ ጥሩ ሚና ሲኖረን መልካም ፖለቲካ ሊኖረን ደካማ አስተዋጾ ሲኖረን ደግሞ ሽባ ፖለቲካ እንደሚኖረን አይጠረጠርም፡፡ ፖለቲካው እማያምረን ከሆነ አስተዋጾዋችንም አለማመሩን ማወቅ ትልቅ ስሌት የሚፈልግ አይመስለኝም፡፡//