አንዳንድ ዜጎቻችን ግብጽ የሰጠችንን የቤት ስራ በአግባቡ እንድንፈጽም ይወተውታሉ$ ለግብጽ እጆቿ ሆነው ተልእኮ ለመፈጸም እያቅማሙ ያሉ እንዳሉ አያለሁ$ በኛ ይሁንባችሁ ግብጽን አንችላትም አርፈን እንቀመጥ ከሚሉን የመክሸፍ ፖለቲከኞች ጀምሮ
የኢትዮዽያ ሰራዊት ግብጽን ከግምት ያስገባ ዝግጅት አላደረገም እስከሚሉን ድረስ ተረኩ አንድና ያው ነው$
ኢህአዴግ ለፖለቲካ ትርፍ እንዳይጠቀም ብሎ መፈክር ማስነገሩ እራሱ ለፖለቲካ መጠቀም መሆኑ
ገሀድ ሆኖ ሳለ ለግብጽ የረጋ ያልረጋ መግለጫ ያልሰጠውን ኢህአዴግን ባልበሰለ ፖለቲካዊ ቁመናው አንድነት ሊመክረው መከጀሉን ሳይ
ሳቅ ቢጤ ከጅሎኝ ነበር$ ምንም ያክል ልዩነት ቢኖር ይሄን አይነቱን የግብጽ ፖለቲከኞች አጉራ ዘለል ባህሪ ለመተቸት
በቀጥታ መናገር እንጂ ነጥብ ለማስመዝገብ በማሰብ የአባይንና የግድቡን ጉዳይ በዚያ መልኩ አውገርግሮ ማቅረብ የወረደ የፖለቲካ ቁመና
ማሳያ ነው$ ይበስላሉ ተብለው ከሚጠበቁ በወጉ ካልተደራጁ ፓርቲዎች በመስማቴ በርግጥ እምብዛም አልገረመኝም$
ያለበቂ ዲፕሎማሲና
ውይይት ያልተጀመረ ግድብ?

