Friday, May 24, 2013

አፍሪካና ህብረትዋ - እሰይ የተጫጫነሽ ድብርት እየለቀቀሽ ነው አብቢልን አፍሪካችን!

አፍሪካ የተበተነች ትልቅ አህጉር ሆና ከርማለች$ ሀብትዋ ያለጠያቂ ሲዘረፍ ኖሯል አልመች ሲል በዲሞክራሲና በሰብአዊ መብት ስም ጦርነት ሁሉ እንዲቀሰቀስ በማድረግ ስትታለብ የኖረች ናት$ ወተቷን አልበው ሌሎች ሲጎነጩት እሷ የራሷን ወተት ተነፍጋ ኖራለች$
 
ከነጻነት ቀጥሎ በነበረው ግዜ ደግሞ የምእራባውያኑ እጅ መጠምዘዣ መሰራርያ ሆነው በስፋት ያገለገሉት ችግር ሁነኛ በሆነ መንገድ ፈተው የማያውቁት የእርዳታ ድርጅቶች ነበሩ$ ምእራባውያኑ እጆቻቸውን በነዚህ በጎ አድራጎት ድርጅቶች በኩል ከስማቸው የራቀ የፖለቲካ ስራቸውን እየሰሩ አህጉሪቱን እያመሱ መንግስታቱን እጃቸውን እየጠመዘዙ የሚሹትን ሀብት ሲቦጠቡጡ ኖረዋል$

እንደነ መለስ ዜናዊ እና ፖል ካጋሜ ያሉ መሪዎች በዋናነት ከሰሩት ስራ ውስጥ መጠቀስ ያለበት ይህን የምእራባውያኑን መጠምዘዣ ሆኖ ያገለግል የነበረውን የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ኔትወርክ መበጠስ ነበር$ ከዚያም አልፎ መለስ ዜናዊ አፍሪካ የፖሊሲ ነጻነት እንዲኖራት በእርዳታ ስም የማይጠቅማትን ፖሊሲ ምርጫ በምእራባውያን መጋት የለባትም በሚል የዋሺንግተን ኮንሰንሰስ በመባል የሚታወቀውን የገበያ አክራሪነት ፍልስፍና በአፍጢሙ ደፍተውታል$

Wednesday, May 22, 2013

አሸናፊነትን ሰበብ አይረታውም


አሸናፊነት ያለሙትን ማሳካት እመረጡበት መድረስ መቻል ነው$ አሸናፊነት እንደ ኳስ ይነጥራል እንጂ እንደ ረጠበ ስፖንጅ እመሬት አይጠፈጠፍም$ አሸናፊ ልምድ በሚወጣም በሚወርድም እርግጫ አይረበሽም$ በቁምነገሩ በራሱ ህይወት ሂደት ሌሎች ያላቸው ፋይዳ ወሳኝ ሚና እንደሌለው ብቻ ሳይሆን ወሳኙን ሚናውን የሚጫወተው ራሱ ብቻ መሆኑን ጠንቅቆ ያውቃል$

አሸናፊ ልምድ ለውድቀቶቹ ሰበብ አይቆጥርም ራሱ እንጂ ሌሎች ሰበቦች ለውድቀቱ መሰረታዊ ፋይዳ እንደሌላቸው ስለሚረዳ$ ሰው ልምድን እንደሚመስል ጠንቅቆ ያውቃል$ ሁዋኝ እንጂ ተደራጊና ተሰሪም እንዳልሆነ አይስትም$ ይሄን ቢስት እንኳ ሀቁ እንደማይቀየር ያውቀዋል$

ህይወት ምርጫ እንደሆነና ያን ምርጫ የማካሄድ ጉዳይ የራሱ ስለመሆኑ እርግጠኛ ነው$ የተሳሳተ ምርጫ በማካሄድ ወይም የመረጠውን ምርጫ በአግባቡ ባለመተግበሩ የሚመጡበትንም ጣጣዎች በጸጋ ዋጥ ያደርጋል እንጂ እነ እገሌ ይህን አድርገው ባይሆን ኖሮ ይሄ ባልሆነ ነበር የሚል ሰበብ አያውቀውም$ እነ እገሌ የማይገባ ነገር እያደረጉም ቢሆን የራሱን ከባቢና ምርጫ የሚያበላሹበትን ሁኔታዎች መቆጣጠር የሱ እንጂ የማንም ሀላፊነት እንዳልሆነ አሳምሮ ያውቃልና$

Monday, May 20, 2013

ህዝባዊ ይሁንታ ተቃዋሚዎችና ኢህአዴግ


እነ Abraha Desta and et el ኢህአዴግ ይሁንታ ወይም ሌጂቲሜሲ የሌለው ስለመሆኑና ኢኮኖሚያዊ እድገት የግዴታ መሟላት ያለበት የመግቢያ ነጥብ እንጂ ምርጫ አሸንፎ ለመቀጠል የማያስችል ስለመሆኑ ነግረውናል። ሲጀመር ኢህአዴግ ህዝባዊ ተቀባይነት እንዲኖረው በአብዛኛው ህዝብ መመረጥ እንጂ በተቃዋሚዎች ወይም በተቃዋሚ ደጋፊዎች መመረጥ ወይም ይሁንታ ማግኘት አይገባውም። ይሄ መቼም ሊሆን አይችልም።

ተቃዋሚዎች ኢህአዴግ ህዝባዊ ይሁንታ የለውም ሲሉን እያሉን ያሉት እኛ መሪ ፓርቲ መሆኑን አልተቀበልንም ከሆነ ትክክል ናቸው። ያ ካልሆነ የህዝቡን ይሁንታማ ህዝቡ በየምርጫው በነቂስ እየወጣ ገለጸኮ። መቼም ህዝብ በነቂስ ወጣም ለማለት እውነቱ ለተቃዋሚዎች ብቻ ሲሆን ነው ካልተባለ።

2ኛው ላነሳው የፈለኩት ቁምነገር ተፎካካሪ ፓርቲዎች ሁነኛ ስራቸው ኢኮኖሚያዊ እድገት ማስመዝገብ እንጂ ሌላ ሊሆን አይችልም የሚለውን ነው። ድህነትን መቅረፍና ተጨማሪ ሀብት መፍጠር ሌላ ምንም ፖለቲካዊ ስራ እንኳ ባይሰራበት ዴሞከራታይዝ የማድረግ አቅም አለው። ምክንያቱን እድገት የሚያመጣቸው ቁሳቁሶችና ሪሶርሶች የማህበረሰቡን መብት የማሳወቅ ለመብቱ እንዲከራከር አቅም የመፍጠር ተፈጥሯዊ ባህሪ አላቸውና።

Thursday, May 16, 2013

ገለልተኛውን ጋዜጠኛና ሚድያ ፍለጋ

አንዳንድ ወዳጆቻችን ሚድያና ጋዜጠኛ አቋም የለሽ ገለልተኛ መሆን አለባቸው አቋምም ይኖራቸው ከሆነ ገለልተኝነታቸው መሆን አለበት የሚል ትርክትና እምነት አላቸው$ አለማቀፍ ተሞክሮው የሚመሰክረው ግን የተለየ ነው$ ብዙ መዘባረቅ ሳያስፈልግ ስመጥሮቹን አለማቀፍ ሚዲያዎች እነ ቢቢሲ አልጀዚራ እና ፍራንስ 24 ብንወስድ ጥቅል የአጀንዳ መረጣቸውና የሚያስተላልፉት መልእክት የየተፈጠሩባቸውን ሀገሮች አላማና የሚከተሉትን የፖለቲካ እምነት የተከተለ ስለመሆኑ አያወያይም$

በቅርቡ የተፈጠረውንና እስካሁንም ያልበረደውን የአረቡን አለም የጸደይ አመጽ አዘጋገባቸውን ብናስተውል ሚድያዎቹ የሚያሰራት ዜና ከሀገሮቻቸው ፖለቲካዊ ጥቅም አንጻር ስለመቃኘቱ የሚያወላዳ ነገር የለውም$ በቱኒዚያና በግብጽ የነበረውን አመጽና ያን ለማስቆም በወቅቱ የነበሩ የሀገሮቹ መሪዎች የሚፈጽሙትን ግድያ ቢቢሲም ይሁን የአሜሪካውያኑ ሚድያዎች ሲያቀጣጥሉት አልነበረም$ ይሄ የሆነው በሁለቱ ሀገሮች መሪዎች የነበሩት ግለሰቦች የምእራባውያኑ ወዳጆች በመሆናቸው ነው$ ሚዲያዎቹ የመንግስቶቻቸውን ወይም የሀገሮቻቸውን አቋም ተከትለው ሲዘምሩ ነበር$ ገለልተኛ አልነበሩም መሆንም አይችሉም$ ሲጀመር ለጽድቅ አልተቋቋሙም ለጥቅም እንጂ$

በዚያው ተመሳሳይ አመጽ ላይ የኳታሩ አልጀዚራ የነበረው ሚና ቀድመን ከጠቀስናቸው ሚድያዎች የተለየ ነበር$ አመጹ የተለየ ስለነበረ ሳይሆን ኳታር የተለየ አላማ ያላት በመሆኑ አልጀዚራም ያን የኳታር የተለየ አላማ ማስፈጸም በሚችልበት አንግል መስራት ነበረበት$ ኳታር በአረቡ አለምም ይሁን በክፍለ አህጉሩ ተጽእኖዋን ማሳደግ የምትሻ በመሆኑ ግዙፏን ግብጽን የሚያዳክም አማራጭ ሲገኝ ያንን በማቀጣጠል ማትፈር ትፈልጋለች$

Wednesday, May 15, 2013

እምነቴ ከሆዴ ስር ውሎ አያውቅም ሆዴም ሀሳቤን እንዲጫነው አልፈቅድም

ይቺ ዬኖክ ስጦታው ስለጋዜጠኝነት ገለልተኝነትና ስለኔ አድርባይነት ለጻፋት የፌስ ቡክ አስተያየቱ ያሰፈርኩለት ማረሚያ ናት፡፡ ኄኖክ ስጦታው ምን መሰለሽ ማወቅ ያለብሽ ገለልተኛ የሚባል ጋዜጠኝነት የለም፡፡ ማረጋገጫ አቅርቢም ቢሉሽ ማጠፊያው ያጥርሻል ለነገሩ ለአሁን አትጨነቂ አላፋጥጥሽም፡፡ እቺን የምትማሩት ከተሳሳተው የጋዜጠኝነት ሀሁ ነው፡፡ 

አቋም ኖሮህ ሲያበቃ ግን ሚዛናዊ መሆን ደፋር መሆን በጨዋ ደንብ ሀሳቦችህን ማቅረብ የሚታየውን እውነት መናገር ይጠይቃል፡፡ የሚመርህን የዚህን አገር ለውጥና የኢህዴግን ስኬቶች ጭምር፡፡ 

በርግጥ አንተ የተቃዋሚዎችን የላሸቀ ቁመና መግለጥና የኢህአዴግን ስኬቶች መናገር ቢቀፍህም፡፡ አንተ የምትተቸው ይሄ ሲቀር ነው፡፡ ለአቋምህና ለአጀንዳህ ማራመጃነት ስለማይሆን፡፡ 

Tuesday, May 14, 2013

አቤት ዘረኝነት

አቤት ዘረኝነት አንድ Dawuro Wisdom የሚባል የፌስ ቡክ ጉዋደኛዬ ራሱን በደበቀባት አካውንቱ ጀርባ ይሄ አገር የዘር ማጥፋት እየተፈጸመበት እንደሆነና ያን ለማስቀረት መፍትሄው ትግሬዎችን ማጥፋት እንደሆነ ነገረኝ፡፡
የለም ይሄ እብደት ነው ዶክተር አማክር ብዬ መከርኩት፡፡

በጣም ተበሳጫና ይሄን ያልከኝ ትግሬ በመሆንህ መሆኑን ፎቶህን ተመልክቼ ደረስኩበት አለኝ፡፡ ቅድም የትግሬዎቹን መገደል አስፈላጊነት አሁን ደግሞ የኔን ትግሬነት ወዲያውና እዛው መሳሳቱና ላርመው ስሞክር መደማመጥ ባለመቻላችን በጨዋ ደንብ ተሰናብቼው ወጣሁ፡፡

ዳውሮ ዊዝደም የሚል ስም የለጠፈው ወዳጄ ግን አሁንም እዚያው ነው የዘር ማጥፋት አማራጩን ዘረኝነትን ከሀገራችን ለማጥፋት እያቀረበልን፡፡ ዘረኛው አፈፍ ብሎ ዘረኛ ሲል የጅራፉን ገርፎ የመጮህ ተረት ያስታውሰኛል፡፡ ለህዝብና ለዴሞክራሲ ያላቸው ቁርጠኝነት ወደ ዘረኝነትና ወደዘር ማጥፋት ከሚወስዳቸው ይሰውረን፡፡

Thursday, May 9, 2013

አከራካሪው የሀገራችን እድገት 1


በሀገራችን ከሚሰሙ ፖለቲካዊ ወቀሳዎች መካከል አንዱ ኢህአዴግ የቁጥር ጨዋታ ስለሚወድ ካልሆነ በቀር ይሄ አገር አላደገም የሚለው ጉልሁ ነውሌላው ባለፉት 20 አመታት የሚጣጣለው ጉዳይ ሀገሪቱ በዴሞክራሲያዊ መብቶች ረገድ የረባ ለውጥ አላደረገችም እንዲያውም ከምርጫ 97 ቀጥሎ ባሉት አመታት ለውጡ የሁዋሊት ተንሸራቷል የሚለው ወቀሳ ነው እነዚህን ክሶች ከመሰረታዊ ጉዳዮች አንጻር መገምገም ይሆናል የዚህ ጽሁፌ ቁምነገር
 
በመሰረቱ እነዚህን አቤቱታዎች ለመቃኘት የመረጥኩት በትምህርት ዘርፍ እየሆ ካለው ነገር በመነሳት ነው መረጃዎች እንደሚያመላክቱትና የተለያዩ አለማቀር ተቁዋማትም ግምገማዎች እንደሚያሳዩት የሀገራችን የትምህርት ሽፋን በአብዛኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች መቶ በመቶ ተሳክቷል ሊባል በሚችልበት ደረጃ ደርሷል 

ቁምነገሩ የትምህርት ሽፋኑ መቶ በመቶ መሆኑ ግን አደለም እኔም በዚህ ቀደዳዬ ማሳየት የፈለኩት ይሄን ስራ የሚመራው ፓርቲ አጀንዳ ይሄን መሰሉን ስራ በመምራት እና በማሳካት ረገድ ምንድነው የሚለውን ማጠየቅ ነው