አፍሪካ የተበተነች ትልቅ አህጉር ሆና ከርማለች$ ሀብትዋ ያለጠያቂ ሲዘረፍ ኖሯል አልመች ሲል በዲሞክራሲና በሰብአዊ መብት ስም ጦርነት
ሁሉ እንዲቀሰቀስ በማድረግ ስትታለብ የኖረች ናት$ ወተቷን አልበው ሌሎች ሲጎነጩት እሷ የራሷን ወተት ተነፍጋ ኖራለች$
ከነጻነት ቀጥሎ በነበረው ግዜ ደግሞ የምእራባውያኑ እጅ መጠምዘዣ መሰራርያ ሆነው በስፋት
ያገለገሉት ችግር ሁነኛ በሆነ መንገድ ፈተው የማያውቁት የእርዳታ ድርጅቶች ነበሩ$ ምእራባውያኑ እጆቻቸውን በነዚህ በጎ አድራጎት ድርጅቶች በኩል ከስማቸው የራቀ የፖለቲካ
ስራቸውን እየሰሩ አህጉሪቱን እያመሱ መንግስታቱን እጃቸውን እየጠመዘዙ የሚሹትን ሀብት ሲቦጠቡጡ ኖረዋል$
እንደነ መለስ ዜናዊ እና ፖል ካጋሜ ያሉ መሪዎች በዋናነት ከሰሩት ስራ ውስጥ መጠቀስ
ያለበት ይህን የምእራባውያኑን መጠምዘዣ ሆኖ ያገለግል የነበረውን የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ኔትወርክ መበጠስ ነበር$ ከዚያም አልፎ መለስ ዜናዊ አፍሪካ የፖሊሲ ነጻነት እንዲኖራት በእርዳታ ስም የማይጠቅማትን
ፖሊሲ ምርጫ በምእራባውያን መጋት የለባትም በሚል የዋሺንግተን ኮንሰንሰስ በመባል የሚታወቀውን የገበያ አክራሪነት ፍልስፍና በአፍጢሙ
ደፍተውታል$
