Thursday, May 30, 2013

Time to give Egypt a lesson


I am saddened to see such arrogance on the part of Egyptian politicians and media. They know for a fact that the dam doesn't harm their interest, they know Ethiopia has all the right to use the water responsibly even for irrigation let alone for electric generation. Yet they try and insight violence where there is none. 


Striking the dam, preventing Ethiopian ships not to use the canal or any other violent option doesn't give Egypt what it wishes. The best solution is to take the negotiations from where they got stalled and move them forward in a way they can come up with win-win solutions. Cooperation is the way out not a single bullet and weapon. 

Friday, May 24, 2013

አፍሪካና ህብረትዋ - እሰይ የተጫጫነሽ ድብርት እየለቀቀሽ ነው አብቢልን አፍሪካችን!

አፍሪካ የተበተነች ትልቅ አህጉር ሆና ከርማለች$ ሀብትዋ ያለጠያቂ ሲዘረፍ ኖሯል አልመች ሲል በዲሞክራሲና በሰብአዊ መብት ስም ጦርነት ሁሉ እንዲቀሰቀስ በማድረግ ስትታለብ የኖረች ናት$ ወተቷን አልበው ሌሎች ሲጎነጩት እሷ የራሷን ወተት ተነፍጋ ኖራለች$
 
ከነጻነት ቀጥሎ በነበረው ግዜ ደግሞ የምእራባውያኑ እጅ መጠምዘዣ መሰራርያ ሆነው በስፋት ያገለገሉት ችግር ሁነኛ በሆነ መንገድ ፈተው የማያውቁት የእርዳታ ድርጅቶች ነበሩ$ ምእራባውያኑ እጆቻቸውን በነዚህ በጎ አድራጎት ድርጅቶች በኩል ከስማቸው የራቀ የፖለቲካ ስራቸውን እየሰሩ አህጉሪቱን እያመሱ መንግስታቱን እጃቸውን እየጠመዘዙ የሚሹትን ሀብት ሲቦጠቡጡ ኖረዋል$

እንደነ መለስ ዜናዊ እና ፖል ካጋሜ ያሉ መሪዎች በዋናነት ከሰሩት ስራ ውስጥ መጠቀስ ያለበት ይህን የምእራባውያኑን መጠምዘዣ ሆኖ ያገለግል የነበረውን የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ኔትወርክ መበጠስ ነበር$ ከዚያም አልፎ መለስ ዜናዊ አፍሪካ የፖሊሲ ነጻነት እንዲኖራት በእርዳታ ስም የማይጠቅማትን ፖሊሲ ምርጫ በምእራባውያን መጋት የለባትም በሚል የዋሺንግተን ኮንሰንሰስ በመባል የሚታወቀውን የገበያ አክራሪነት ፍልስፍና በአፍጢሙ ደፍተውታል$

Wednesday, May 22, 2013

አሸናፊነትን ሰበብ አይረታውም


አሸናፊነት ያለሙትን ማሳካት እመረጡበት መድረስ መቻል ነው$ አሸናፊነት እንደ ኳስ ይነጥራል እንጂ እንደ ረጠበ ስፖንጅ እመሬት አይጠፈጠፍም$ አሸናፊ ልምድ በሚወጣም በሚወርድም እርግጫ አይረበሽም$ በቁምነገሩ በራሱ ህይወት ሂደት ሌሎች ያላቸው ፋይዳ ወሳኝ ሚና እንደሌለው ብቻ ሳይሆን ወሳኙን ሚናውን የሚጫወተው ራሱ ብቻ መሆኑን ጠንቅቆ ያውቃል$

አሸናፊ ልምድ ለውድቀቶቹ ሰበብ አይቆጥርም ራሱ እንጂ ሌሎች ሰበቦች ለውድቀቱ መሰረታዊ ፋይዳ እንደሌላቸው ስለሚረዳ$ ሰው ልምድን እንደሚመስል ጠንቅቆ ያውቃል$ ሁዋኝ እንጂ ተደራጊና ተሰሪም እንዳልሆነ አይስትም$ ይሄን ቢስት እንኳ ሀቁ እንደማይቀየር ያውቀዋል$

ህይወት ምርጫ እንደሆነና ያን ምርጫ የማካሄድ ጉዳይ የራሱ ስለመሆኑ እርግጠኛ ነው$ የተሳሳተ ምርጫ በማካሄድ ወይም የመረጠውን ምርጫ በአግባቡ ባለመተግበሩ የሚመጡበትንም ጣጣዎች በጸጋ ዋጥ ያደርጋል እንጂ እነ እገሌ ይህን አድርገው ባይሆን ኖሮ ይሄ ባልሆነ ነበር የሚል ሰበብ አያውቀውም$ እነ እገሌ የማይገባ ነገር እያደረጉም ቢሆን የራሱን ከባቢና ምርጫ የሚያበላሹበትን ሁኔታዎች መቆጣጠር የሱ እንጂ የማንም ሀላፊነት እንዳልሆነ አሳምሮ ያውቃልና$

Monday, May 20, 2013

ህዝባዊ ይሁንታ ተቃዋሚዎችና ኢህአዴግ


እነ Abraha Desta and et el ኢህአዴግ ይሁንታ ወይም ሌጂቲሜሲ የሌለው ስለመሆኑና ኢኮኖሚያዊ እድገት የግዴታ መሟላት ያለበት የመግቢያ ነጥብ እንጂ ምርጫ አሸንፎ ለመቀጠል የማያስችል ስለመሆኑ ነግረውናል። ሲጀመር ኢህአዴግ ህዝባዊ ተቀባይነት እንዲኖረው በአብዛኛው ህዝብ መመረጥ እንጂ በተቃዋሚዎች ወይም በተቃዋሚ ደጋፊዎች መመረጥ ወይም ይሁንታ ማግኘት አይገባውም። ይሄ መቼም ሊሆን አይችልም።

ተቃዋሚዎች ኢህአዴግ ህዝባዊ ይሁንታ የለውም ሲሉን እያሉን ያሉት እኛ መሪ ፓርቲ መሆኑን አልተቀበልንም ከሆነ ትክክል ናቸው። ያ ካልሆነ የህዝቡን ይሁንታማ ህዝቡ በየምርጫው በነቂስ እየወጣ ገለጸኮ። መቼም ህዝብ በነቂስ ወጣም ለማለት እውነቱ ለተቃዋሚዎች ብቻ ሲሆን ነው ካልተባለ።

2ኛው ላነሳው የፈለኩት ቁምነገር ተፎካካሪ ፓርቲዎች ሁነኛ ስራቸው ኢኮኖሚያዊ እድገት ማስመዝገብ እንጂ ሌላ ሊሆን አይችልም የሚለውን ነው። ድህነትን መቅረፍና ተጨማሪ ሀብት መፍጠር ሌላ ምንም ፖለቲካዊ ስራ እንኳ ባይሰራበት ዴሞከራታይዝ የማድረግ አቅም አለው። ምክንያቱን እድገት የሚያመጣቸው ቁሳቁሶችና ሪሶርሶች የማህበረሰቡን መብት የማሳወቅ ለመብቱ እንዲከራከር አቅም የመፍጠር ተፈጥሯዊ ባህሪ አላቸውና።

Thursday, May 16, 2013

ገለልተኛውን ጋዜጠኛና ሚድያ ፍለጋ

አንዳንድ ወዳጆቻችን ሚድያና ጋዜጠኛ አቋም የለሽ ገለልተኛ መሆን አለባቸው አቋምም ይኖራቸው ከሆነ ገለልተኝነታቸው መሆን አለበት የሚል ትርክትና እምነት አላቸው$ አለማቀፍ ተሞክሮው የሚመሰክረው ግን የተለየ ነው$ ብዙ መዘባረቅ ሳያስፈልግ ስመጥሮቹን አለማቀፍ ሚዲያዎች እነ ቢቢሲ አልጀዚራ እና ፍራንስ 24 ብንወስድ ጥቅል የአጀንዳ መረጣቸውና የሚያስተላልፉት መልእክት የየተፈጠሩባቸውን ሀገሮች አላማና የሚከተሉትን የፖለቲካ እምነት የተከተለ ስለመሆኑ አያወያይም$

በቅርቡ የተፈጠረውንና እስካሁንም ያልበረደውን የአረቡን አለም የጸደይ አመጽ አዘጋገባቸውን ብናስተውል ሚድያዎቹ የሚያሰራት ዜና ከሀገሮቻቸው ፖለቲካዊ ጥቅም አንጻር ስለመቃኘቱ የሚያወላዳ ነገር የለውም$ በቱኒዚያና በግብጽ የነበረውን አመጽና ያን ለማስቆም በወቅቱ የነበሩ የሀገሮቹ መሪዎች የሚፈጽሙትን ግድያ ቢቢሲም ይሁን የአሜሪካውያኑ ሚድያዎች ሲያቀጣጥሉት አልነበረም$ ይሄ የሆነው በሁለቱ ሀገሮች መሪዎች የነበሩት ግለሰቦች የምእራባውያኑ ወዳጆች በመሆናቸው ነው$ ሚዲያዎቹ የመንግስቶቻቸውን ወይም የሀገሮቻቸውን አቋም ተከትለው ሲዘምሩ ነበር$ ገለልተኛ አልነበሩም መሆንም አይችሉም$ ሲጀመር ለጽድቅ አልተቋቋሙም ለጥቅም እንጂ$

በዚያው ተመሳሳይ አመጽ ላይ የኳታሩ አልጀዚራ የነበረው ሚና ቀድመን ከጠቀስናቸው ሚድያዎች የተለየ ነበር$ አመጹ የተለየ ስለነበረ ሳይሆን ኳታር የተለየ አላማ ያላት በመሆኑ አልጀዚራም ያን የኳታር የተለየ አላማ ማስፈጸም በሚችልበት አንግል መስራት ነበረበት$ ኳታር በአረቡ አለምም ይሁን በክፍለ አህጉሩ ተጽእኖዋን ማሳደግ የምትሻ በመሆኑ ግዙፏን ግብጽን የሚያዳክም አማራጭ ሲገኝ ያንን በማቀጣጠል ማትፈር ትፈልጋለች$

Wednesday, May 15, 2013

እምነቴ ከሆዴ ስር ውሎ አያውቅም ሆዴም ሀሳቤን እንዲጫነው አልፈቅድም

ይቺ ዬኖክ ስጦታው ስለጋዜጠኝነት ገለልተኝነትና ስለኔ አድርባይነት ለጻፋት የፌስ ቡክ አስተያየቱ ያሰፈርኩለት ማረሚያ ናት፡፡ ኄኖክ ስጦታው ምን መሰለሽ ማወቅ ያለብሽ ገለልተኛ የሚባል ጋዜጠኝነት የለም፡፡ ማረጋገጫ አቅርቢም ቢሉሽ ማጠፊያው ያጥርሻል ለነገሩ ለአሁን አትጨነቂ አላፋጥጥሽም፡፡ እቺን የምትማሩት ከተሳሳተው የጋዜጠኝነት ሀሁ ነው፡፡ 

አቋም ኖሮህ ሲያበቃ ግን ሚዛናዊ መሆን ደፋር መሆን በጨዋ ደንብ ሀሳቦችህን ማቅረብ የሚታየውን እውነት መናገር ይጠይቃል፡፡ የሚመርህን የዚህን አገር ለውጥና የኢህዴግን ስኬቶች ጭምር፡፡ 

በርግጥ አንተ የተቃዋሚዎችን የላሸቀ ቁመና መግለጥና የኢህአዴግን ስኬቶች መናገር ቢቀፍህም፡፡ አንተ የምትተቸው ይሄ ሲቀር ነው፡፡ ለአቋምህና ለአጀንዳህ ማራመጃነት ስለማይሆን፡፡ 

Tuesday, May 14, 2013

አቤት ዘረኝነት

አቤት ዘረኝነት አንድ Dawuro Wisdom የሚባል የፌስ ቡክ ጉዋደኛዬ ራሱን በደበቀባት አካውንቱ ጀርባ ይሄ አገር የዘር ማጥፋት እየተፈጸመበት እንደሆነና ያን ለማስቀረት መፍትሄው ትግሬዎችን ማጥፋት እንደሆነ ነገረኝ፡፡
የለም ይሄ እብደት ነው ዶክተር አማክር ብዬ መከርኩት፡፡

በጣም ተበሳጫና ይሄን ያልከኝ ትግሬ በመሆንህ መሆኑን ፎቶህን ተመልክቼ ደረስኩበት አለኝ፡፡ ቅድም የትግሬዎቹን መገደል አስፈላጊነት አሁን ደግሞ የኔን ትግሬነት ወዲያውና እዛው መሳሳቱና ላርመው ስሞክር መደማመጥ ባለመቻላችን በጨዋ ደንብ ተሰናብቼው ወጣሁ፡፡

ዳውሮ ዊዝደም የሚል ስም የለጠፈው ወዳጄ ግን አሁንም እዚያው ነው የዘር ማጥፋት አማራጩን ዘረኝነትን ከሀገራችን ለማጥፋት እያቀረበልን፡፡ ዘረኛው አፈፍ ብሎ ዘረኛ ሲል የጅራፉን ገርፎ የመጮህ ተረት ያስታውሰኛል፡፡ ለህዝብና ለዴሞክራሲ ያላቸው ቁርጠኝነት ወደ ዘረኝነትና ወደዘር ማጥፋት ከሚወስዳቸው ይሰውረን፡፡

Thursday, May 9, 2013

አከራካሪው የሀገራችን እድገት 1


በሀገራችን ከሚሰሙ ፖለቲካዊ ወቀሳዎች መካከል አንዱ ኢህአዴግ የቁጥር ጨዋታ ስለሚወድ ካልሆነ በቀር ይሄ አገር አላደገም የሚለው ጉልሁ ነውሌላው ባለፉት 20 አመታት የሚጣጣለው ጉዳይ ሀገሪቱ በዴሞክራሲያዊ መብቶች ረገድ የረባ ለውጥ አላደረገችም እንዲያውም ከምርጫ 97 ቀጥሎ ባሉት አመታት ለውጡ የሁዋሊት ተንሸራቷል የሚለው ወቀሳ ነው እነዚህን ክሶች ከመሰረታዊ ጉዳዮች አንጻር መገምገም ይሆናል የዚህ ጽሁፌ ቁምነገር
 
በመሰረቱ እነዚህን አቤቱታዎች ለመቃኘት የመረጥኩት በትምህርት ዘርፍ እየሆ ካለው ነገር በመነሳት ነው መረጃዎች እንደሚያመላክቱትና የተለያዩ አለማቀር ተቁዋማትም ግምገማዎች እንደሚያሳዩት የሀገራችን የትምህርት ሽፋን በአብዛኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች መቶ በመቶ ተሳክቷል ሊባል በሚችልበት ደረጃ ደርሷል 

ቁምነገሩ የትምህርት ሽፋኑ መቶ በመቶ መሆኑ ግን አደለም እኔም በዚህ ቀደዳዬ ማሳየት የፈለኩት ይሄን ስራ የሚመራው ፓርቲ አጀንዳ ይሄን መሰሉን ስራ በመምራት እና በማሳካት ረገድ ምንድነው የሚለውን ማጠየቅ ነው

Wednesday, May 8, 2013

መብታችን በምልአት ይከበር

ከሰሞኑ ህገመንግስቱ እንዲከበር የሚጠይቁ ድምጾች በርክተዋል$ የምር እንዲህ ያለው ጥረት መደገፍ ያለበት ነው$ መብታችን ሳይሸራረፍ እንዲከበር መታገል ይኖርብናል$ በዚህ የማህበራዊ ሚድያ ዘመቻ ጥቂት ግለሰቦች የምር ህገመንግስቱ ተሙዋልቶ እንዲከበር እንደሚፈልጉ አምናለሁ$

ይሄን ዘመቻ በዋናነት የሚያቀነቅነው ቡድን ግን ሊያስተውላቸው የሚገቡ መሰረታዊ ነጥቦች በመኖራቸው እነዚያን ማንሳት የግድ ይላል$ ሲጀመር መከበር ያለበት መብት አንቀጽ 30 ብቻ አደለም$ መከበር ያለበት ሁሉም አንቀጽ ነው- 106ቱም አንቀጽ$

ይሄ ህገመንግስትን የማክበር ጉዳይ በተቀመጠው ህጋዊ መንገድ እስካልተቀየረ ድረስ የተቃዋሚዎቻችን ራስ ምታት ለሆነው አንቀጽ 39ም የሚሰራ ይሆናል ማለት ነው$ ይሄ የሰላማዊ ሰልፍና ሀሳብን በነጻ የመግለጽ ጉዳይ በተናጠል ለምን እንደሚቀነቀን አይገባኝም$ መብታችን ሳይሸራረፍ የሚከበረው ህገመንግስቱ በምልአት ሲከበር እንጂ ለወቅታዊ አጅንዳ የምትፈለግን አንቀጽ በማንጠልጠል አይመስለኝም$

መንግስት ህገመንግስቱ ይከበር ብሎ ሲሰራ ህገመንግስቱን ህገ አራዊት የሚሉትና ሰላማዊ የትግል አማራጮች በመዳፈናቸው ያለን አማራጭ አመጽ ብቻ ነው የሚሉን ወዳጆቻችን ደርሰው ለህገ መንግስቱ ተቆርቁዋሪ ሲሆኑ ከበስተጀርባው ያንጠለጠሉት ህገወጥ አንቀልባ እንደሚኖር ብንጠረጥር የሚነወር አይመስለኝም$

በዚያ ላይ መብታችን ሳይሸራረፍ ይከበር በሚል አጀንዳ ስር የተሸረፉ ሁለት አንቀጾቻችንን አንጠልጥሎ ያለወትሮው ለህገመንግስቱ ቀንደኛ ደጋፊ ሆኖ ለመታየት የሚሞክርን ቡድን ቆም ብሎ መገምገም በምንም መስፈርት ከበቅሎ ራስ ቀንድ እንደ መፈለግ የሚቆጠር አይመስለኝም$

ደግ ይሁን ይሄም የህገመንግስቱ አካል ነውና እንዲከበር መስራት ይገባል$ ግን ይሄ ቡድን ከቀናት በፊት ሲፈጽም የነበረውን አዋራጅ ተግባሩን እንዴት ዘንግቶት ነው ለሀገርና ህገመንግስት እንደሚቆረቆር ሀገር ወዳድ ብቅ ያለው? አባይ ፕሮፖጋንዳ ነው አይሰራም እየተሰራም አደለም ይልቁንም ባለስልጣኖቹ ኪሳቸውን ሊያደልቡ የፈጠሩት ማወናበጃ ነው ያሉን አደሉም ወይ?!

አይናችን ስር እየበቀለ ያለውን ከደማችን የወፈረውን የአባይን ጉዳይ የካዱንና ያንኑ ለመገንባት የሚሰባሰበውን ገንዘብ ለማስቆም ያልተሳካ ግን አዋራጅ የሀገር ክህደት ከሚፈጽሙ ቡድኖች ጋር ይሰራ የነበረ ቡድን መሆኑን ስናስብ የዚህ አላማ ያልተሳካውን በፌስቡክና በትዊተር አመጽ ለመፍጠር ሲደረግ የነበረውን ጥረት ለማንሰራራት የሚደረገው ጥርጊያ አካል እንደሆነ አንስተውም$

ብዙዎቹ ይሄንን ጥረት የሚያቀነቅኑት ግለሰቦችና ይሄ መልእክት የሚተላለፍባቸው የፌስቡክ አካውንቶች በሀገሩ ላይ ክህደት ለሚፈጽመውና ከግብጽ ጋር ለመስራት ከሚጥሩ ቡድኖች ጋር በመተባበር የሚያሰራጫቸውን ሀሳቦች ስናስታውስ አጀንዳው ህገመንግስት የማስከበር ጉዳይ ሳይሆን አመጽ ለመፍጠር ቀዳዳ ይፈጥሩልናል የሚሉዋቸውን ህገመንግስታዊ ድንጋጌዎች ለነውጥ የማመቻቸት ጉዳይ መሆኑን መገመት ከባድ አደለም$

ይሄን የምለው አንዴ የተሳሳተ አይታረምም የሚል ደንጋራ አተያይ ስላለኝ ሳይሆን ይሄን አቁዋም ባራመዱበትና ሀገራዊ ክህደት በፈጸሙበት የሳምንት እድሜ በማይሆን ግዜ ከስህተታቸው ትምህርት ወስደው አተያይና ስነምግባራቸውን የመቀየር በቂ ግዜና አጥጋቢ ምክንያት ስለማይታየኝ ነው$

እንዲያውም አዋራጁን ሀገራዊ ክህደታቸውን ለማረሳሳትና አጀንዳ ለመቀየር የሚያደርጉት ጥረት አካል አድርጌ ነው የማየው$ በአባይ ግድብ ላይ የፈጸሙት ክህደት ታሪክ የማይረሳው ሆኖ ይቀጥላል$ ይቅርታ የምናደርግላቸው ቢሆንም የተግባራቸው አዋራጅነትና የፈጸሙት የሀገር ክህደት ግን የማይዘነጋ ክስተት ሆኖ ይኖራል$

ወዳጆቻችን ቁምነገሩ አጀንዳ ማስቀየር አደለም$ በተግባር የባህርይ እና የአመለካከት ለውጥ ማድረግ ነው$ የተከናነባችሁት ኪሳራም አጀንዳ በመቀየር የሚጠግግ አይነት እንዳደለ እናንተም አትስቱትም$ ይሄን አንድና ሁለት የማይዋጥላቸውን አንቀጽ ጠቅሰው ህገአራዊት የሚሉትን ህገመንግስት እንዴት ደርሰው ተቆረቆሩለት የምንለው ይሄን በተደጋጋሚ ሀገር የካደ አካሄድና አመለካከት ስለምናውቅ ነው$

ይሄ ህገመንግስት በመቃብሬ ላይ ካልሆነ በቀር በአመጽ ማንም አየቀይረውም እያለ ኢህአዴግ ለህገመንግስቱ ያለመሸራረፍ መከበር ሲከራከር እኒህ የህገመንግስት ነቢያት እውን የት ነበሩ?! ወይስ የሚደግፉት ፓርቲ ስለተቃወመው ያኔ አንገታቸውን ደፍተው ነው!?

የህገመንግስቱ ጠበቃ ኢህአዴግ የህገመንግስቱ ባለቤት ኢህአዴግ በህጉ ተጠቃሚው ኢህአደግ አድርገው የሚስሉት ተቃዋሚዎች ደርሰው ዛሬ በአመዛኙ ቃል አቀባዮቻቸው በሆኑ የፌስቡክ ወዳጆቻችን በኩል ይሄን ህገመንግስታዊ ጥብቅናቸውን ሲያሰሙን ያ ለ20 አመት የጸና ደንዳና ተቃዉሞ እንዴት ተኖ ነው ብንል አይፈረድብንም$  

ለነገሩ ቁምነገሩን አልሳትነውም መብታችን ተሙዋልቶ ይከበር የሚሉን አንድና ሁለት አንቀጽ ጠቅሰው መሆኑን ስንታዘብና እነዚያንም አንቀጾች አምነውባቸው ሳይሆን ሊበሉዋት የፈለጉዋትን ቆቅ ሆኖባቸው እንደሆነ ይገባናል$ እነሱ ሲሰለፉ ሀገር ለመጉዳት ያልተጋበዙበትን ስብሰባ ለመበጥበጥ ጭምር ሲሰለፉ መብታቸው ሆኖ ሌላው አቁዋሙን በሰልፍ ሲገልጽ ሆዳምና ተገዶ የወጣበት ሆኖበት እንዲሚያደርጉት እና ያኔ እንደሚቃወሙት አንስተውም$

ይሄ የፌስቡክ ዘመቻ ህገመንግስታችን ሳይሸራረፍ በምልአት ይከበር በሚልና ሁሉንም አንቀጾች በሚያንጸባርቅ መልኩ ሲካሄድ እንደ ኢህአዴግ ሁሉ ሁሉም ቡድን በመቃብሬ ላይ ካልሆነ ይሄ ህገመንግስት በአመጽ አይቀየርም የሚል የጸና አቁዋም ሲያራምድ ያኔ ድመቱዋ የመነኮሰችው ጥፍሩዋን የምር ቆርጣው መሆኑ ይገባናል$

እቺ ማጨናበሪያ የአባዩን መዋጮ ለማስቀረት ሞክሮ የበለጠ መገለል የገጠመው አክራሪ ተቃዋሚ የፈጠራት የተጠናች ዘመቻ መሆኑዋን ስለምናውቅና ስለምታውቁት ግድየለም በሽፍንፍን ትቅርባችሁ$

በርግጥ ግን የምር ሁላችንም የህገመንግስታችን ተቆርቁዋሪ ብንሆን የሚያኮራ ይሆናል$ ይሄ እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ$ ይቆየን!

Marching or Innovating?

It hasn't been essentially the streets that have developed matured democracy and development in America or Europe; it is the how they maximize their freedom. They were busy innovating and working hard to make life easier.

Most of them were devoting themselves to make the best of their rights for work and property than their rights to march. 

To march needs only pain, to bring about solutions seeks innovation, long study and experiment hours and persistence to make remedies for pains. Do the greatest thing, which is to solve.

Marching and shouting your frustration is not bad; but it is a way of showing difference; it has not been solution to any development or democratic failure.

Why don't we get firmly involved in making things happen than seeking others to make it happen for us. To march is to demand, to innovate and to make the solutions is to provide what the public seeks.

Be provider of solutions than being person of the streets.