Monday, December 30, 2013

የአማራው፣ የኦሮሞው እና የትግሬው ዘረኛ ትረካዎች--- ክፍል 2



=======================
በዚህ ትንታኔዬ የኔ የሚባሉትንም ከመተቸት ወደሁዋላ አላልኩም። እውነታውን በጋራ መጋፈጥና በሀቀኝነት ችግሩን ፈተን ሁላችንም በጥረታችን ልክ አሸንፈን እና እኩል ተጠቃሚ ሆነን የምንኖርበት አገር ካልፈጠርን መዘዙ አደገኛ ነው ብዬ ስለማምን የሚመስለኝን ሁሉ ድፍረትና ሚዛናዊነትን አጣጥሜ ላቀርበው ሞክሬያለሁ። መልካም ንባብ።

ስጀምር በኔ አተያይ እንደ ብሄራችን የታሪክ ትረካችን ይለያያል። ታሪኩን እምንዘክርበት ስሜትና ወግም በዚያው ልክ የተለያየ ነው። አንዱን ታሪካችንን ከደማችን እየቀዳን እያነበብን ብዙ አይነት አድርገን ግራ እንጋባለን፣ ግራ እናጋባለን።

ጥቅል ድምዳሜዬን የሚጎሉትን ጉዳዩች ሞልታችሁ እንደምታነቡ በማመን ለኔ እንደሚታየኝ ከሶስቱ ብሄሮች፦ ኦሮሞ፣ አማራና ትግሬ የሚወለዱ የታሪክ ነጋሪያን እና አመስጣሪዎች እንዴት ታሪካችንን እንደሚያነቡት ላስረዳ።
===================
1 የአማራው ታሪክ ተንታኝ፦

የአማራው ታሪክ ተንታኝ በአመዛኙ የኢትዮዽያን ታሪክ የኔ ብሎ የሚያስብ፥ በሀገሪቱ በተካሄዱ መሰረታዊና ወሳኝ ጉዳዩች ላይ የራሱ ብሄር የተለየ ግዙፍ ሚና አለው ብሎ የሚያስብ፥ በመሆኑም በተነጻጻሪ አማራ ስልጡን ብሄር ነው ብሎ የሚያምን እና ለዚህ ተወልጄበታለሁ ለሚለው ብሄሩ አገር ግንባታ ታሪካዊ ሪከርድ ተጋድሎ ለመፈጸም የቆረጠ፥ ማን እንደኛ እያለ ማስረዳት እሚቃጣው፥ በዚህም የተነሳ ራሱን የተሻለና የዚሁ የተሻለው ታሪክ አድራጊና ፈጣሪ አድርጎ የሚያስብ ሆኖ የቆየ ነው።

አማራው እኮ ማለት የሚቀናው በቀጥታም አዙሮም የብሄሩን ታላቅነት ለመስበክ ወደሁዋላ የማይል ነው። የዚህን አገር ታሪክ የማንነቱ መገለጫና የአማራነቱ ክፋይ አድርጎ ስለሚያይ ብሄራዊ ማንነቱን ከታሪኩ ለይቶ ማየት የተሳነው ሊባል ይችላል። ይሄን ታሪክ ሊጠይቅ የሞከረውን ሁሉ ሀገራዊ ፍቅር የሌለው፣ ገንጣይ አስገንጣይ እያለ የሚፈርጅ ነው። የታሪክ አሳሳሉ ደግሞ አድናቂ እና አወዳሽ ከመሆን አይዘልም።

የዚህ የአማራ ታሪክ ተራኪ መሰረታዊ ስህተቶች ሁለት እንደሆኑ እረዳለሁ። አንደኛው የሀገሪቱን ታሪክ የአማራ ታሪክ ብሎ መውሰዱና ሁለተኛ ደግሞ የአማራን ማንነት እና ትልቅነት ከዚህ ታሪክ መወድስ ጋር አሰናስሎ የሰፋው መሆኑ ነው።

አማራው ከዚህም ታሪክ ጋር ይሁን አይሁን ክቡርነቱ እንዲያው ከተፈጥሮ እንደማንኛውም ህዝብ የሚቀዳ መሆኑን አይረዳም። በመሆኑም ለዚህ የታሪክ መምህር ታሪኩን መንካት አማራን መንካት፤ ይህን የሱን የታሪክ ትርክት አለመቀበል የአማራን የበላይነት እና የተሻሌነት አለመቀበል አድርጎ ይወሰደዋል። በቀጥታ ማንነቴ ተነካ ግን አይለንም። ሀገሬን ኢትዮዽያን የነካ እምዬ ኢትዮዽያን የደፈረ በሚል መፈክር ይህን የታሪክ ትርክት የተቹትን ያሳድዳል። ያኔም አሁንም።

በመሆኑም በኔ እምነት ሀገራዊ ታሪክ ሀገራዊ አንድነት እና ብሄራዊ ማንነቱ የተምታቱበት በመሆኑ የሌላውን የታሪክ ትርክት ለመስማት እንኳ እድል የማይሰጥ ይመስላል።

ንጉስ ሚኒሊክ ቅኝ ገዢ ወይስ ከፊውዳሎች እንደ አንዱ--- ክፍል 1




በመጀመሪያ ጉዳዩን ማየት የምፈልግበትን መነሻ ላስቀምጥ። አላማዬ ታሪካዊ ትንታኔ መስጠት አደለም። አላማዬ ታሪክ የምናጣቅስበትን መነሻና እሚመራበትን አተያይ መፈተን ነው። ለእናንተም በዚህ ንባብ ቃል እምገባው በየትኛውም ወገን ሆነን የሰማነውን ታሪክ መነሻ አላማና ግቡን እንድትጠይቁት የሚጠቁሙ ቁምነገሮች እንደማካፍላችሁ ነው።

ሀገራችን ከየት ናት? የመቼ ናት?

ሀገራችን የብራና መጻፍ ወይም አመተምህረት መጥቀስ ሳያስፈልግ ከሰሜን እስከ ደቡብ ህዝቡ ተሳስሮ የሚገኝበት አሰፋፈር አንዴ አንዱ ሲያይል ወደ ሰሜን ሲዘምት፤ ኦሮሞ ጎንደር ላይ ሆኖ ሲያስተዳድር እስከዛው ድረስ ያለውን ህዝብ በጦርነት ረምርሞት ሄዶ እንደነበር ይናገራል። እስከ ዛሬ ጎንደር ላይ የምናያቸው ስያሜዎችና አብያተ ክርስትያናት እና የኦሮሞ ባህልና ቋንቋ ያላቸው ማህበረሰቦች የሚያመላክቱት ያን ነው። በወሎ በኩልም የእያንዳንዱ ገጠርና ወንዝ አካባቢ ስም ሳይቀር በኦሮምኛ ተሰይሞ የምናገኘው በአጋጣሚ አደለም። አካባቢውን ይዞት ኖሮበት መርቶት እንደነበር የሚያሳይ ነባራዊ ሀቅ ነው። አሁንም ድረስ ኦሮምኛ የሚናገሩ የወሎ አካባቢዎች የዛ ዋቢዎች ናቸው። እስከ ትግራይ የኦሮሞ ባህል እና ደም አሻራዎች ዛሬም አሉ። እናም ሀገር አንዴ በሰሜኖቹ ተዋጊዎች ሌላ ግዜ ደግሞ በደቡቡ ጀግኖች ስትመራ ስትገብር የኖረችበት ሁኔታ ነበር። ሀገር አንዴም በደቡቦቹ ጭካኔ ሌላ ግዜ ደግሞ በሰሜኖቹ ጭካኔ ስትደማ ስትበለት ስትቆረጥ ነበር። 

የታሪክ ድርሳናት የቅርቡንም የሩቁንም ታሪክ ሲያወጉ የወንድ ብልትና የሴት ጡት ቆርጦ ወደ መጣበት አካባቢ በመውሰድ ጀግንነቱን የሚያስመሰክር ጦረኞች እንደነበሩ ይዘክራሉ። የገደልንም እኛው የተጋደልንም እኛው ማን ምንገደለ እንዴት ገደለም ብለን የምንነታረክ እኛው ነን። ታሪካዊ ሀቆቹን መቀየር አይቻልም። ሀቆቹን መካድም ፋይዳ የለውም።

ወሎ ካሳሁን ሁሴን የሚባል ሙስሊም ብቻ ሳይሆን መሀመድ ሀይለጊዮርጊስ አምባቸው ጉደታ የሚባልም ሰው ያለበት አካባቢ ነው። ስም እየጠራህ ስትሄድ ሀይማኖት ብቻም አደል የሚደባለቀው ዘሩም ድብልቅ ይሆንብሀል። ይሄን አገር በወጉ ካየነው ቋንቋዎቹ የሚያሳዩንን ልዩነት ሀይማኖቶቹ የሚያሳዩኑን መስመር እና ብሄራዊ ጥንቅሩ የሚያሳየንን ልዩነት ታሪካችንን የሁዋሊት እየተረተርነው ስንሄድ አናገኘውም።

Monday, November 11, 2013

The government is always wrong even in the Saudi case


#Every time there is a problem #gov't should be blamed@ the working policy
#Every time there is a problem #Seek solutions@ that is the winning policy

Given this, when I consider our discourse on a number of issues, whenever a problem emerges in Ethiopian political, economic and social sphere, the best thing we do is blame each other as if it were order of God.

Problems seek solutions, not further problems and altercations on them. Of course, this is a typical nature of defeated mind-set. Winning minds want to see ways to solve; ways to cooperate minds and resources to interdependently solve the problem with better efficacy and quality.

What is wrong with us that we often choose to quarrel about the problems than managing to look for credible solutions? Time to heal this bad habit before it gets irreversible.

Every time there is a problem, we don't see how we can cooperate to solve the problem. We don't use our creative power to best cooperate to deal with the actual problem.

#‎Saudi‬ Arabia ‪#‎They‬ are right to torture, rape, kill us#

It is true the Arabs have petroleum; they have got the money with it. But they don't develop their mind as they have developed their petroleum fields with Western expertise.

These tragedies are the result of undeveloped mind, mind that sit on dollar purse. The problem with money is while it gives you choices to make, it doesn't at all discern the wrong from the right and it doesn't make for you the right choice morally or financially.

People that don’t develop wealth in their own nation have to go through torture, rape and killing. That is the beauty of poverty. Poverty can only be solved when wealth is created. But the best we, especially the youth, are doing is producing a pile of criticism and hate notes while these poor people is seeking for tangible solutions for century long tangible, killing, torturing and raping problems.

Friday, October 11, 2013

ፖለቲካችን አጓጓን ወይስ አስቄመን



ፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ የሚያቀርቡ ሲሆኑ ህዝብ በአዲስ ጉጉት ይወጠራል፡፡ በአዲስ ተስፋ ይሳባል፡፡ አዲሱ ምርጫ ስቦት ነባሩን ገዢ ፓርቲ በአዲስ ስለመተካት ያሰላስላል፡፡ ቃል የተገባለት የተሻለ ነገር አሁን ያለውን ጥሩ አማራጭ ለመተካት ያነሳሳዋል፡፡ ይሄኔ ነው ማጓጓት የሚቻለው፡፡ ይሄኔ ነው አማራጭ መኖሩ የሚታወቀው፡፡ ጉጉት የተሻለ ነገር ከመናፈቅ የሚፈጠር ስህበት ነው፡፡

እንዲህ ያለ የሚያጓጓ አማራጭ ባለበት መከፋትን በመጠንሰስ ቂም በቀል በማስረጽ የሆን ተብሎ ተበደልክ ተገለልክ ስብከት በማስለፈፍ ድጋፍ መፈለግ ይከስማል፡፡ ቁምነገሩ ለሀገራዊ ችግሮች መፍትሄ መፈለግ ያን የሚያሳካው መንገድ ደግሞ የተዋጣላት እና በወጉ የተቀመረ ፕሮግራም ይሆናል፡፡

እሚያጓጓ ፕሮግራም ያበጀ ፓርቲ በተበዳይነት ስሜት (ቪክቲም ሜንታሊቲ) ወይም በቂም በቀል ፖለቲካ የሚጣድበት ምንም ምክንያት ስለማይኖረው አብይ አጀንዳው ሳቢና አስተማማኝ ፕሮግራሙን በስፋት በማስተዋወቅ ድጋፍና የምርጫ ካርድ መግዛት እንጂ ሌላ ሊሆን አይችልም፡

ይህን መሰሉን በራስ መተማመን እና ልምድ የተላበሰ ፓርቲ ማቋቋም ደግሞ የበሰሉ ፕሮግራሞችን መንደፍ ሀገራዊ ውርደቶቻችንን የመቀየር እና ሀገራዊ ድሎቻችንን የማስቀጠል በመሆኑ በዋናነት ከተቃውሞ ጋር ሳይሆን ሀገራዊ መፍትሄዎች እና ሀብት ፈጠር አቅሞች ከማዳበር ጋር ይሰናሰላል፡፡

በመሆኑም ሆድ የማስባስና ተፎካካሪ ፓርቲን የማስጠላት ድውይ ፖለቲካ ዋናኛ መነሾ አማራጭ አልባ ሆኖ በጥላቻ ፖለቲካ ተመርዞ ፖለቲካውን መቀላቀል ነው፡፡ ይህን መሰሉ ፖለቲካ ለሀገራቸው ሀገራዊ ችግሮች መፍትሄ ለመፈለግ ሳይሆን በፖለቲካ መድረኩ ላይ ለሚያዩዋቸው ግለሰቦች ያላቸውን ጥላቻ ለመግለጽ በሚገቡ ግለሰቦች የሚፈጸም ነው፡፡

ፕሮግራም የሌለው ቡድን ደግሞ የሚቃወመውን ቡድን ፕሮግራም እያነሳ ከማላዘን የተሻለ አማራጭ ሊኖረው አይችልም፡፡ ቂም በቀልና ጥላቻ የመዝራት ተልእኮ ይዘው በፖለቲካው መድረክ የሚርመሰመሱ ቡድኖች አብይ መገለጫም ይሄው ነው፡፡ ማጣጣል ማሳበብ መውቀስ ይህን መሰሉን ወሬ ነጋ ጠባ መደጋገም እና ይሄው የፖለቲካ ፕሮግራም ሆኖ ኢህአዴግ ባያጭበረብር ኖሮ በዝረራ ይሸነፍ ነበር እያሉ መጎረር ነው አጀንዳቸው፡፡

በመሆኑም የበሳል ፖለቲካ አንዱ መገለጫ ለሀገራዊ ችግሮች ያበጃቸውን መፍትሄዎችና ለሀገራዊ ሀብቶች መፍጠርያ ያበጃቸውን አማራጮች በማስተዋወቅ ህዝብ በፕሮግራሞቻቸው በመተማመን በሚልቀው አማራጫቸው ጉጉት አነሳሽነት እንዲመርጣቸው ማስቻል ነው፡፡

ይህን መሰሉን ባህሪ በማዳበር እንዲህ አይነቱን ባህሪ የሚያላብስ ፕሮገራም በመቅረጽ ኅዝብን በጉጉት የሚስቡ ፓርቲዎች ለማግኘት መብቃት ይገባል፡፡ ይቻላልም፡፡ ቁምነገሩ በሀገራዊ ችግሮቻቸን መፍትሄ እና ሀብት ፈጠራ ዙርያ ለመስራት መሰባሰብ መቻል ነው፡፡

Tuesday, October 8, 2013

#‎አማራጭ‬ ፓርቲ #አማራጭ ፕሮግራም ነው



የፖለቲካ ፓርቲ ብዝሀነት አብይ አላማ ለአንድ ሀገር ህዝቦች የተለያዩ የፖለቲካ አማራጮችን ማቅረብ ነው፡፡ የተቃውሞ ፖለቲካ ከገዢ ፓርቲ አንጻርም ከተመዘነ ሌላ አጀንዳ ሊኖረው አይችልም:: ገዢ ፓርቲው እያስገኘ ካለው ስኬት የተሻሉ ስኬቶች ማስመዝገብ የሚችሉ የፖሊሲ አማራጮች የፖሊሲ አማራጩ እምብዛም ልዩነት ከሌለው ደግሞ የተሻለ የመፈጸም አቅም እና ስነምግባር ያለው ፓርቲና አባላት በማደራጀት ህዝቡ ይህን በመሰለው ፓርቲ አማራጭ የማስፈጸም አቅም ዙርያ መተማመን እንዲፈጥር ማድረግ ነው፡፡

ይህን በመሰለ አማራጭም ሰከን ብሎ ገዢ ፓርቲን መርታት በሂደትም ጠንካራ ዴሞክራሲያዊ ፖለቲካዊ ስርአት መመስረት ይቻላል፡፡ ይህን መሰሉን ጠንካራ ፖለቲካዊ ስርአት ለማቋቋም ደግሞ ቀስ በቀስ ጠንካራ ዴሞክራሲያዊ እሴቶችን መፍጠር ተገቢ ነው፡፡

ያን የመሰሉ እሴቶች የሚኖሩን ሰከን ያሉ አማራጮች በማቅረብ የተጠመዱ ፓርቲዎችና መልእክቶቻቸው እኒህን አማራጮች በማስተዋወቅ ዙርያ ያጠነጠኑ ፓርቲዎችን መገንባት የቻልን እንደሆነ ነው፡፡ በወሳኝነት ይህን የመሰለ ቁመና የሚኖራቸው ፓርቲዎች አብይ ስራ ውስጣዊ ቁመናቸውን ማነጽ የጠሩ ፕሮግራሞችን መንደፍ በነደፏቸው ፕሮግራሞች ዙርያ መልእክቶች ማበጀት እነዚሁኑ መልእክቶች በትጋት በማሻሻጥ ላይ ያተኮሩ ይሆናሉ፡፡

ያኔ ነው በሂደት በህዝቡ እምነት እየተቸራቸው አማራጮቻቸው መወያያ እየሆኑ የአባሎቻቸው ቁመና ከሌሎች አባሎቸ ቁመና አኳያ እየተመዘነ በእንድ በኩል የዳበሩ ብቁ ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉበት የተለያዩ አቋሞች የሚራመዱበት ዴሞክራሲያዊ እሴቶቹ የጎለበቱበት የፖለቲካ ብዝሀነት በሌላ ጎኑ ደግሞ ይህን በመሰለው ሂደት አቀጣጣይነት የዳበረ የማገልገል መንፈስ አፈጻጸም እና ልማት የሚስተዋልበት መንግስታዊ እና ድርጅታዊ መዋቅሮች እየተገነቡ የሚሄዱበት ሁኔታ ይፈጥራል፡፡

አሁን ያለውን ሁኔታ ስናጤን ግን ከስልሳ እስከ 90 የሚደርሱ ፓርቲዎች እናስተውላለን፡፡ ይሄ ግን ተመሳሳይ ቁጥር ባለው አማራጭ የተተረጎመ አደለም፡፡ ከአማራጮች ይልቅ የፓርቲዎቹ ቁጥር የሚያመላክተው በተለያዩ ቡድኖች የተሰባሰቡ ግለሰቦችን በፖለቲካ ስም የመነገድ ጥቅሞች የማጋበስ ፍላጎት ነው፡፡ ስንኩዋንስና ዘጠና በኛ የፖለቲካ መድረክ የለየላቸው ጥርት ባሉ ፖለቲካዊ አይዲዮሎጂና ፍልስፍና የሚመሩ 2 ወይም 3 አማራጮች አናይም፡፡

እየተዘጋጀ ካለ መጽሀፍ የተቀነጨበ

አዋጭ ፖለቲካዊ ባህርያት



  • ጎደለ ወይስ ሞላ
ፖለቲካ በአማራጮች ሲዋጅ እስከ ግማሽ ጎዶሎ ነውን በእስከ ግማሽ ሙሉ ነው ይተካል፡፡ ይሄ የአባባል ለውጥ አደለም፡፡ የአጀንዳ ለውጥ ነው፡፡ ሊሞላ ሊጨምር እና ሊያሳካ የሚመኘው ያንንም ለማሳካት የቀረጸው ፕሮግራም ያለው በመሆኑ ስለጎደለው ሳይሆን እንደሚሞላ ስለሚተማመንበት እና ዝግጅት ስላደረገበት ጉዳይ በማንሳት ይጠመዳል፡፡
በራስ መተማመኑ የሚመነጨው በባላንጣው ጉድለቶች ላይ ሳይሆን በራሱ ጥንካሬዎች ላይ በመሆኑ ስለጎደለው ሳይሆን የቀረው ስለሚሞላበት አግባብ እና ያን ለመሙላት ስላደረገው ዝግጅት በማስረዳት ላይ ነው የሚያተኩረው፡፡

ስለሚሞላው ነገር ምንነት ስለጉድለቱ መነሻዎች እና ሊሞሉት ስለሚችሉ ቁሳቁሶች ምንነት ያን እንዴት እንደሚያፈላልግ እና እንደሚያሟላ ስትራቴጂክ ትልሞቹን እየነገረ ስለሚሞላው ነገር በአባላቱ በደጋፊዎቹና በጥቅል ማህበረሱ ላይ እምነት እየፈጠረ ይሄዳል፡፡

ለእንደዚህ አይነት ፓርቲዎች ጉድለት መንጠላጠያ የትችት ማዝነቢያ ሰንሰለት ሳይሆን በአማራጭ ፓርቲነት የቀረበው ቡድን መፍትሄ የሚፈልግለት ተጨባጭ መመዘኛው መሆኑን አይስትም፡፡ ለዚህ ተጨባጭ ክፍተትም መፍትሄ በመፈለግ ድርጅታዊ ብቃቱን ለጉድለቶች መሙያ የሚሆኑ መፍትሄዎችን እና መላዎችን ማቅረብ እንደሚችል ያረጋግጣል፡፡
ይሄ ድርጅታዊ የመሙላት አቅም እና ዝግጁነት ነው አንድን ፓርቲ አማራጭም ተመራጭም ሊያደርገው የሚችለው፡፡ 

በመሆኑም ኢህአዴግ መሙላት ስላልቻለ እና ጎዶሎ ስላለበት ምረጡኝ ከማለት ወደ የመፍትሄው ባለቤት ነኝ ላልተሞሉት ችግሮች መፍትሄ ያበጀሁላቸው በዚህ አግባብ ነው ጉድለቶቹም የተፈጠሩት በነዚህ መነሻዎች መሆኑን ለይቻለሁ ሊሞሉ የሚችሉትም በዚህ አግባብ ስለመሆኑ ይህን የመሳሰሉ መረጃዎች አሉ በሚል ይቀርባል፡፡

ያኔ ስለጎደለ ልምረጥ ማለት ይቀርና የመሙያውን ቁልፍ የያዝኩት እኔ ስለሆንኩኝ ምረጡኝ ወደሚል በሁለት እግሩ የቆመ አማራጭ ይወስደናል፡፡ በመሆኑም አማራጭ ፓርቲዎች ጉድለቶችን መፍትሄ የማፈላለጊያ አማራጭ የመጠቆሚያ ተጨባጭ መነሻዎች እንጂ የወቀሳ መንጠላጠያ አያደርጓቸውም፡፡

እግረ መንገድ ግን እንዴት ሙሌቱን እንደሚፈጥሩ ሲያመላክቱ ገዢው ፓርቲ ቀዳዳዎቹን እንዴት እንደፈጠረ ወይም ሊለያቸው እንዳልቻለ ከየትኛዎቹ ፕሮግራሞቹ ወይም ፖለቲካ ፍልስፍናዎቹ እንደሚመነጩ ከፓርቲው ፍልስፍና እንኳ የማይመነጩ ከሆኑ ደግሞ እንዴትና ለምን ጉድለቶቹን ሊሞሏቸው እንዳልቻለ በመጠቆም ከገዢውም ከሌሎቹም ፓርቲዎች ለምን የተሻለ አማራጭ እንደሆኑ ሊያመለክቱ ይችላሉ፡፡

ዋናው ነገር ግን መፍትሄ ማበጀት መቻላቸው እና ሙላት የሚሆኑ ሀሳቦች አሰራሮች እና ፕሮግራሞች ያሉዋቸው መሆናቸውን ማስተዋወቅ በመሆኑ በራሳቸው ጥንካሬና ፕሮግራም ዙርያ አተኩረው የጎደለውን የሚሞሉ እንጂ በጎደለው ሰበብ የስልጣን ርካቡን የሚንጠላጠሉ አለመሆናቸውን ማስረገጣቸው ነው፡፡

ስለጉድለት አውስተው የሚወዳደሩ ሳይሆኑ በሚሞላው መፍትሄ መሆን በሚችለው ተወዳዳሪ ፖሊሲዎች ፕሮገራሞች እና አደረጃጀታቸው ተጫርተው በተሟላ የህዝብ እምነት ለመፍትሄው ወደስልጣን የሚመጡ መሆናቸው ነው፡፡
ይህን ለመሰሉ ፓርቲዎች ጥማታቸው ወንበር አደለም፡፡ ጥማቸው ሀገራዊ መፍትሄ መበጀቱ ነው፡፡ በዚህ ሂደት መፍትሄውን ማበጀት የሚችል ቡድን በህዝብ ሀላፊነት እስከተሰጠው ድረስ የስልጣን ጥማቸው ሆዳቸውን በልቷቸው ለነሱ መሰልጠን ሲባል ሰላማዊው ሂደት እንዳይደፈርስ በጽናት የሚቆሙ ናቸው፡፡ ውድድሩን ፖለቲካዊ ምህዳሩን የሚመዝኑት በውድድሩ አሸናፊ በመሆናቸው ሳይሆን ውድድሩ ዴሞክራሲያዊ  እሴቶችን ሊያንጽ በሚችል አግባብ እየተመራ ነው ወይስ አደለም በሚል ሚዛን ይሆናል፡፡

መሞላቱ ነው ቁምነገሩ፡፡ መፍትሄው ነው ዋናው ነገር፡፡ መፍትሄው እየተቀመረ እስከሄድ ድረስ ፖለቲካዊ ስልጣን መያዝ አለመያዝ የፖለቲካ ተሳትፏቸው መመዘኛ አደለም፡፡ ተሳትፏቸውን ማስገኘት በቻለው ጥቅል ፖለቲካዊ ጥቅምና እሴት ግንባታ እንጂ በታገሉለት ወይም በሚታገሉበት ፓርቲ ስልጣን ቆይታ ወይም መያዝ አደለም ማለት ነው፡፡

Tuesday, September 3, 2013

ኢትዮጵያ እንዳትገነጣጠል- ክፍል ሁለት




ክፍል አንድ ካነሳናቸው ጉዳዩች የሚለጥቁ ራስን ማስተዳደር እንደ መለያያ ስትራቴጂ 1983 ሀገራችን የሚሉና ሌሎች ጉዳዩችን የሚዳስሰው የጹሁፉን ሁለተኛ ክፍል እነሆ

መብት እንደ ጥርጣሬ መፍጠርያ

አንዳንዶች ራስን በራስ የማስተዳደር መብት የተከበረው ይሆነኝ ተብሎ ህዝቦችን ለማንኳሰስና በመሀላቸው ጥርጣሬ ለመፍጠር ነው የሚል ክስ ያቀርባሉ፡፡ አለመተማመኑን ኢህአዴግ የሚፈልገው ወጥና ጠንካራ ተቃውሞ እንዳይገጥመው ነው በሚል ክሱን ያጠናክራሉ፡፡ ይህ ደግሞ እድሜውን ለማራዘም ያገለግለዋል ብለው ያምናሉ፡፡


አንደኛ በተፈጥሮአዊ ባህሪያቸው እነዚህ ህገመንግስታዊ ድንጋጌዎች እንዴት ነው አለመተማመን የሚፈጥሩት ብሎ መጠየቅን ያሻል፡፡ በየክልሉ ያሉ የተለያዩ ብሔሮች ሰሜኖች እየመሩን የሚኖሩት እኛ ራሳችንን ማስተዳደር ተስኖን ነው ወይ በሚል ቁጭት የሚንገፈገፉበትን ጉዳይ ነው የመለስው፡፡ በርግጥም ትክክል ናችሁ አዎ ራሳችሁን ማስተዳደር ትችላላችሁ ሰሜኖቹም የማስተዳደር ስራውን ለናንተ እንዲያስረክቡ ህገመንግስቱ በሚጠይቀው መሰረት ተደርጓል ነው የሚለው፡፡ ሰሜኖቹም የማስተዳደር ተፈጥሯዊ አቅምና መብት አላቸው አካባቢያቸውን በዚያው መሰረት ያስተዳድራሉ የሚል ፍትሀዊ ድንጋጌ ነው፡፡


ይሄ በርግጥም የመብቶችን በተሟላ መንገድ መከበር ይገልጻል እንጂ በምን ሚዛን ነው ጥርጣሬ በህዝቦች መካከል የሚያነግሰው፡፡ በመላው ሀገሪቱ ፍትሀዊ ነው ተብሎ ሊወስድ ቢችል እንጂ በምንም ሚዛን መጠላላት እና ጥርጣሬ የሚከስት ሆና አላገኘውም፡፡ በባህሪው ያን የማድረግ አቅም የለውም፡፡


ይልቅ ለአካባቢው ማህበረስብ የማስተዳደር ሀላፊነቱ ሲመለስ ከዚያ ቀድሞ በነበረው ግዜ በአመራር ቦታው ላይ የነበሩ ሰዎች የመሪነቱን ቦታ ሲያጡ አብሮ የሚደርቅ እና የምረዳው የሚያጡት ጥቅም ይኖር ይሆናል፡፡ ያ በቤተሰብ እና በግለሰቦች አንጻር ሲመዘን ጉዳት እንዳለሁ እረዳለሁ፡፡ ግን ድንጋጌው ከሚያስገኘው ጥቅም አንጻር እና ነጻነት ከሚያጎናጽፋቸው መላው የኢትዮጵያ ብሄሮች አኳያ ሲመዘን እዚህ ግባ የሚባል ጉዳይ አደለም፡፡ የለውጡም አላማ ይህን የመሰሉ ግለሰቦች ጥቅም ማሳጣት ሳይሆን ራሱን የመምራት ተፈጥሮአዊ ብቃት ያለውን ህዝብና ዜጋ መብት ማክብርና ማስከበር ነው፡፡


በዚህ ሂደት አማራው የተጎዳ በማስመሰል ለማቅረብ የሚሞከርበት አዝማሚያ ሌላው ነው፡፡ በጋሞ ጎፋ አርባምንጭ ተወልዶ እንዳደገ አማራ የሆነውን አውቀዋለሁ፡፡ በአመዛኙ ከሰሜን እና ከሸዋ በመጡ ሰዎች የተያዘው የሀላፊነት እና የመሪነት ቦታ በአካባቢው ተወላጆች ተወስዷል፡፡ ያ ግን በዋናነት የሚያሳየው የአካባቢው ሰው የስልጣን ባለቤት መሆኑን እንጂ ይሆነኝ ተብሎ በቀድሞዎቹ መሪዎች እና ዜጎች ላይ የደረሰን በደል አደለም፡፡


አማራውም ትግሬውም ሸዌውም በአካባቢው ራሱን የመምራት መብት እንደ ተጎናጸፈ ኁሉ ሌላውም ብሄር ራሱን የመምራት ሀላፊነትን እንደ መብትነቱ መጎናጸፉ ምንም ክፋት የለውም ብቻ ሳይሆን ተገቢና ትክክል ነው፡፡ ምን ያክል እርካታም በጋሞጎፋ ተወላጆች ዘንድ እንደፈጠረ አውቃለሁ፡፡


መተቸት ያለበት እንዲህ ያለውን ራስን የመምራት ሃላፊነት በአካባቢው በሚኖሩ ሌሎች ብሄሮች ተወላጆች ላይ ጉዳት እና አድሎ ለማድረስ የሚጠቀሙበት ሀላፊዎች እና ሌሎች የአካባቢው ተወላጆች የሚኖሩ ከሆነ ነው፡፡ እንዲህ አይነት ሰዎች እንዳይኖሩ ማድረግ የሚቻል ባይመስለኝም እንዲህ አይነት ጠባብ አመለካከታቸውን ሲተገብሩት ያለርህራሄ ማድረቅ ግን ያስፈልጋል፡፡

ኢትዮጵያ እንዳትገነጣጠል- ክፍል አንድ


ባለፈው ግዜ ከነጃወር የተንሸዋረረ የማንነት እና የዜግነት ጥያቄ በመነሳት እቺ አገር ያለችበትን ሁኔታ የሚዳስስ ጽሁፍ ለማቅረብ ቃል ገብቼ ነበር፡፡ በዚያው መሰረት ሀገራችን ሳትገነጣጠል ልትቆይ የሚያስችላትን አማራጭ በኔ እይታ አቅርቤዋለሁ፡ እንምከርበት እንሟገት፡፡

እንደ መግቢያ
በጥሬው ኢትዮጵያ እንዳትገነጣጠል ማሰብና በአንድነት አጽንቶ በእድገት አልቆ ሊያስቀጥል የሚችል ስርአትና አመራር መፍጠር የተለያዩ ናቸው፡፡ አብዛኛው ኢትዮጵያዊ አንድነቱን የሚመርጠው መሆኑ አነጋጋሪ አደለም፡፡ አንድነት ተጠብቆ ሊዘልቅ የሚችልበትን አማራጭ በመምረጥ ረገድ ግን ልዩነቶች ይስተዋላሉ፡፡


በወሳኝነት በፖለቲካው መድረክ ከዚህ አኳያ የሚፋለሙት አስተሳሰቦች ሁለት ናቸው፡፡ አንዱ ኢህአዴግ ያቀረበው ራስን በራስ የማስተዳደር እስከ መገንጠል አማራጭ ሲሆን ሌላኛው የተወሰኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚያቀነቅኑት በብሄር ሳይሆን በጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ እንዲተዳደሩ የሚለው አማራጭ ነው፡፡ ይህ አማራጭ ከክልሎቹ መዋቅር እስከ ፌደራል መንግስት መዋቅር ባህርያት ድረስ ቁርጥ ያሉ አማራጮች ያበጀ አይመስልም፡፡ በግርድፉ የሚያቀርበውን ሀሳብ ግን እንየው፡፡


ጂኦግራፊያዊ የፌደራል ስርአት አማራጭ
እንደ ኢዴፓ ያሉ ይህን አማራጭ የሚያቀርቡ ፓርቲዎች ህዝብ ብሄራዊ ማንነቱ ከግምት ሳይገባ እንደ አቀማመጡ አመቺነት ወሎ ጎጃም ሲዳማ ሀረርጌ አይነት ብለን  እንደ አመቺነቱ እናስተዳድር የሚል አማራጭ አይነት ነው የሚያቀርቡት፡፡ አማራጩ በርግጥ ጥርት ባለ መልኩ ተብራርቶ ባይቀርብም እነ ልደቱን ከመሳሰሉ ፓለቲከኞች ከሰማሁት ገለጻ ተነስቼ ስናገር በጂኦግራፊ ተከፍሎ ሲያበቃ የብሄሮችን በገዛ ቋንቋቸው የመጠቀም መብት ግን ያከበራል ይላሉ፡፡


በተጨማሪም የመሪዎች ምርጫ በህዝቡ የሚካሄድ ስለሚሆን በጂኦግራፊ መከፈሉ ችግር አያመጣም ይላሉ፡፡ ይሁንና ይህ አይነቱ ውሳኔ እንደ ኦሮምያ ሶማሊያና አፋር ለመሳሰሉ በርካታ ሌሎች ብሄሮች አርኪ መልስ አይመስልም፡፡ ምክንያቱም ራሳቸውን በራሳቸው የማስተዳደር ጥያቄ ዋናው የማንነት እና የእኩልነት ጥያቄ ነውና፡፡ ይህ አማራጭ አጀንዳውን ተራ የፌደራል ስርአት የመመስረት እንጂ ከማንነት ራስን ከማስተዳደርና ከእኩልነት አንጻር ከሚነሱ ጥያቄዎች ጋር በማስተሳሰር ያጤነው አይመስልም፡፡


እንዲያውም ይህ አይነቱ አተያይ በጠባብ ከባቢያዊ አስተሳሰብ ድጋፍ ለሚሰበስቡ ፓለቲከኞች የሚያበረታታ አጀንዳ የሚፈጥርላቸው ይመስላል፡፡ የመገንጠል አጀንዳ የሚያቀነቅኑትም ዛሬም ቢሆን ራስህን ማስተዳደር ያልተፈቀደለህ ስለማትታመን ነው ዛሬም መብትህ አልተከበረም በሚል ዝማሬ ለማነሳሳት ይጠቀሙበታል፡፡ በጣም ቢዳከሙም ዛሬም መሰል የመገንጠል አስተሳሰቦች የራስ አስተዳደር በተከበረበትም ሲራመዱ የምንታዘበው ይህን የህዝቡን ፍላጎት ጠምዞ ለአጀንዳቸው ለማዋል ታስቦ መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡

መፍትሄ ፈብራኪ ወይስ ወቀሳ ጠማቂ


ነጻ የወጣ ህሊናና ህዝብ አብይ ተግባር ኢኮኖሚያቸውን መቀየር ነው፡፡ ዲትሮይቶቹን እና ሲሊካን ቫሊዎቻቸውን ማነጽ፡፡ ነጻነታቸው ከሚያስጀምሯቸው ሁነኛ ጉዳዮች መካከል ዋነኞቹ ኢኮኖሚያዊ ናቸው፡፡ የፖለቲካ ነጻነትም አብይ ፋይዳ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ማስገኘት መቻሉ ነው፡፡ የህዝብ አብይ ጥያቄዎች ዞሮ ዞሮ ኢኮኖሚያዊ ናቸውና በተለይ እንደኛ ባለ ደሀ ሀገር፡፡ የፖለቲካ ጥያቄዎችም አብይ ፋይዳ ኢኮኖሚያዊ ነጻነቶችን ማረጋገጥ መቻል መሆኑ ይታወቃል፡፡


ኢኮኖሚውን ማንደርደር ወይስ ፓለቲካውን ማንተክተክ
በብዙ መልኩ ሲመዘን የኛ ሀገር ፖለቲካ ያለበት ደረጃ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዩችን ወደፊት በመግፋት ላይ የሚያተኩር ሳይሆን በመብት ላይ የተንጠለጠለ ከመብትም ደግሞ በተሟላ መንገድ ያሉ ጭብጦች ላይ ሳይሆን በየወቅቱ ከሚወጡ ደንቦችና ህጎች ውስጥ በተወሰኑ ለወቀሳ ያመቻሉ በሚባሉ በወጉ ባልተላመጡ ጉዳዩች ላይ ተንተርሶ ገዢውን ፓርቲ ለማጣጣል ከመሞከር ባለፈ በሀራችን የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች ፕሮግራሞቻቸውን በወጉ በተጠኑ ሀገራዊ ጉዳዩች ዙርያ የማያደራጁ በየወቅቱ በሚኖሩ ክርክሮች ላይ ራሳቸውን ከማስተዋወቅ ይልቅ በድክመትም ቢሆን እያነሱ ሲያስተዋውቁ የሚውሉት ኢህአዴግን  የሆነብት ሁኔታ ነው ያለው፡፡


በዚህ ሂደት የፖለቲካውን ሙቀት ከመጨመር በዘለለ ምናልባትም በተወሰኑ ጉዳዩች ላይ ገዢውን ፓርቲ ከማብጠልጠል ባለፈ በሀገሪቱ ወሳኝ ስለሆነው የኢኮኖሚ እድገት ወዴትነት እንዴትነት በምን አማራጭ ሊያድግ እንደሚችል በማመላከት ረገድ እዚህ ግባ የሚባል ግብአት እስከማይኖራቸው ደርሰዋል፡፡


በዚህ የተነሳ በኢኮኖሚው ላይ ፓርቲዎቹ የሚሰጡት ትንታኔ ግለሰቦች ከሚሰጡት የአሉባልታ ትንታኔ የተሻለ ብስለት የማይታይበት እና ወትሮም ገዢው ፓርቲ እያሳደገው ያለውን ኢኮኖሚ እንዴት በላቀ የእድገት ምጣኔ እንደሚያሳድጉት ሊያመላክቱን ቀርቶ አሁን ባለውም ቁመናው እንዴት እንደተደራጀ ምን ለውጥ እያስገኘና ምን እጥረቶች እየፈተኑት እንዳሉ እንኳ በወጉ የማይገነዘቡ ፓርቲዎች የተጠራቀሙበት ምህዳር በመሆን ቀጥሏል፡፡


ይሄ የሆነው እና እየሆነ የቀጠለው ተቃዋሚዎቹ ወደ ፖለቲካው ጎራ ከተፍ የሚሉት አንድም በፖለቲካ ፓርቲ መሰባሰብ ያስገኛል የሚሉትን ጥቅም ለመቀራመት በሌላም ይህ ካልሆነ ደግሞ ኢህአዴግን በሚረባም በማይረባም ጉዳይ ስለሚጠሉት ብቻ ይሆንና ተቃውሞ የጥላቻ መልእክት ከመቀመር እና አቤቱታ ከመዘመር የተሻለ ቁምነገር የሌለው ሆኖ ያርፋል፡፡ ለዚህ ነው የሀገራችን የተቃዉሞ ፖለቲካ ከአቤቱታ ከፍ የሚል ሚና መጫወት የተሳነው፡፡

እዚህ አገር ብዙ ችግር አለ




አዎ እዚህ አገር ችግር አለ፡፡ ችግሩን ደግሞ በየእለቱ በየሰአቱ በየደቂቃው እየኖርነው ነው፡፡ በአንድ በኩል የመሰረተ ልማት እጦቱ መሰረተ ልማቱ ሲኖርም በአግባቡ አለመስራቱ የሚፈጥርብንን ምሬትና ጉዳት በሌላ በኩል በየለቱ የሚሞቱት ሕጻናት እና እናቶች በየግዜው መመገብ ያልቻልናቸው ነገሮችና ልናገኝ ያልቻልነው የህክምና አገልግሎት የበለጠ ያሳምመናል በቀላሉ፡፡ ልናገኝ ስንችል ያላገኘነው መንግስታዊም ግለሰባዊም አገልግሎት ይጎዳናል ያስመርረናልም፡፡


ቁምነገሩ ግን እንደማንኛውም አንድ ግለሰብ ማማረርና የችግር አለ ትርክት ማሳመርና ማስዋብ አደለም፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና በፖለቲካውና በኢኮኖሚው በንቃት የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች ሁነኛ ሀላፊነት የችግሩን ምንጭ በአስተማማኝ ጥናት መለየት ምንጮቻቸው ለታወቁ ችግሮች ተገማች እና ሳይንሳዊ መፍትሄ መቀመር እና ይሄው መፍትሄ ተተግብሮ እሚፈለገው ለውጥ እንዲገኝ ማድረግ ነው፡፡


ከመደበኛው ማህበረሰብ እኩል ችግር አለ እያሉ ለማስተጋባት ከሆነ በፓርቲ ደረጃ የምንሰባሰበው ይሄ ፋይዳ የለውም፡፡ መሰባሰብ እንደ ፓርቲ መቆም የፖለቲካ አጀንዳ ነድፎ መንቀሳቀስ ጠቃሚ የሚሆነው መደበኛው ግለሰብ አጥንቶ ሊደርስባቸው የማይችላቸውን ጉዳዩች በተደራጀ መልኩ አከናውኖ ችግሮች የሚፈቱበትን አግባብ የሚቀመር ከሆነ እንጂ ከመደበኛው ግለሰብ እኩል ችግር አለ ለማለትማ በፓርቲ ደረጃ መሰባሰብ አያስፈልግም፡፡ ያንማ ሰለማዊ ሰለፈኛም ያደርገዋል፡፡ ቁምነገሩ መፍትሄውን አፈላልጎ ማግኘት በዚያ ዙርያ ድጋፍ አሰባበስቦ ሕዝብን አሳምኖ ምርጫ ማሸነፍና የመሪነቱን ሚና ተቀብሎ ሕዝብ ይገባዋል የምንለውን ጥቅም ማሳካት መቻል ነው፡፡


በምን ስሌት ነው ችግር አለ ብሎ የምናውቀውን ችግር ስለተረከልን አንድን የፖለቲካ ድርጅት ሀገር የመምራት ሀላፊነት የምንሰጠው፡፡ ጥያቄው የመፍትሄ እንጂ የችግሮች መኖርን ክሽን ባለ ቋንቋ የማቅረብ ያለማቅረብ ጉዳይ አደለም፡፡ ችግር እንዳለ ኑሯችንን ጠቅሰው አስረዱን እንበል ይሄን ማድረጋቸው የሚባለውን ችግር የመፍታት ሁነኛ መነሻውን የመለየት እና የተበጀውን መፍትሄ የመተግበርና የማስተግበር ድርጅታዊ አቅማቸውንና አቋማቸውን ሊያሰየን ይችላል እንዴ? አይችልም፡፡ የፓርቲ ሁነኛ አላማም ህዝብ የሚማረርበትን ችግርና አሁን ካለው ቁመና አንጻር ወደፊት ሊገጥሙት የሚችሉትን ተገማች ተግዳሮቶች በመተለም ችግር የሚፈታና ሀብት መፍጠር የሚችል አመራር መስጠትና ማስተግብር እንጂ ችግር ተራኪ ድምጽ መሆን አደለም፡፡

የፖለቲካ ሀላፊነት እንደ ችግር መፍቻ ቃልኪዳን




አንድ የፖለቲካ ፓርቲ ለህዝብና ለደጋፊዎቹ የሚገባው ቃልኪዳን ለውጥ ነው፡፡ በተገማች እና በሳይንሳዊ ዘዴዎች መመላከት ማሳመን ማነሳሳት የሚችሉ የለውጥ ቃልኪዳኖች፡፡ እንዲህ ያለ ቃልኪዳን መግባት ደግሞ አላማ ይጠይቃል፡፡ ሀገር የመለወጥ አላማ፡፡ ሀገር ለመለወጥ የተነሳሳ በዚያው አላማ ዙርያ መሸ ጠባ ሊተጋ ይገባል፡፡ ይህን በመሰለ አላማ ዙርያ የማይሰራ ያን ማሳካት የሚችሉ ጥቅል ፍልስፍናዎች ከዚያ የሚቀዱ የረጅም ግዜ የመካከለኛና የአጭር ግዜ እቅዶች ነድፎ በነዚያ ዙርያ ህዝቡ ግንዛቤ እንዲኖረው የማይተጋ ፓርቲ የሚቀረው መንጠልጠያ ትችት ብቻ ነው፡፡ ትችት ጌጡ ሆኖ የሚያርፈው እንዲህ አይነት ትልም የሌለው ፓርቲ ነው፡፡


ይሄን መሰሉ የፓርቲ ቁመና የጠራ አላማ እና ከአላማ ለአፍታም ቢሆን አይንን አለመንቀል ይጠይቃል፡፡ እንዲህ ባለ ትኩረት የሚሰራ ቡድን በርካታ የሚያቅዳቸው የሚያነሳ የሚጥላቸው ጉዳዩች ስለሚኖሩት ስለራሱ በማውራት የራሱን ፕሮግራም በማነጻጸር ይጠመዳል፡፡ የሌሎቹን ተፎካካሪ ፓርቲዎችም አማራጮች አዋጭ አለመሆን የሚያነሳው አማራጩን ሲያስተጋባ በማሳያነት ወይም በማነጻጸሪያነት ሲያነሳው እንጂ ነጋ ጠባ ስለባላንጣው ሲያወራ የሚከርምበት ሁኔታ ሊኖር አይችልም፡፡


ስለ ባላንጣቸው በማውራት የሚጠመዱ ፓርቲዎች ዋነኛ ችግር ስለባላንጣቸው ያላቸው የከፋ ጥላቻ አደለም፡፡ ትልቁ ችግር ለሀገራቸው የሚያቀርቡት አማራጭ ራእይ የሌላቸው መሆኑ ነው፡፡ አጀንዳ ያለው ቡድን ስለሌሎች ለማውራት ግዜ አይኖረውም፡፡ በሚያገኛት የተወሰነች የሚዲያ አጋጣሚ የፓርቲዉን መልእክት በማስተላለፍ ስራ ላይ ብቻ ይጠመዳል፡፡ በተቃራኒው ላይ የሚያተኩር ቡድን ውድቀት እንደ ፓርቲ የሚታገልበት ጥርት ያለ አላማ እና የተተነተነ እቅድ አለመኖር ነው፡፡

Saturday, August 31, 2013

#Wahabi/Salafi trends in Ethiopia # its Tactics

They preach the radical wahabi/salafi doctrine to prepare the ground for radicalism in Ethiopia

When the government tell them to stop their radicalization and take the right route, they accuse the government for preaching Ahbash, another moderate sect like Sufi Islam, which is the form of Islam, Muslims practice in the country for so long

They try and snatch the leadership by force in mosques to effectively plot their radical agenda all over the country; when they are told to work with in the rule of the land and peacefully
they simply turn and accuse the government for interfering in their religion as if they are religious and as if they represent the millions of Muslims across the country.

Wednesday, August 28, 2013

እውን ኤርትራን ማን አንገት አደረጋት?

ኤርትራ ክብር የሚገባቸው ሕዝቦች መኖሪያ መሆኗ እንደተጠበቀ ሆኖ የራሷን ጉዳይ በራሷ መወሰን ያለባት ሀገር መሆኗ እንደተጠበቀ ሆኖ ሲያበቃ አንገት የሚያደርጋት ቁመና ያላት ግን አደለችም፡፡ ወደብም ኤርትራን አንገት አያደርጋትም፡፡ ምናልባት አንገት ትሆን የነበረው ኢትዮጵያውያን ከአሰብ ወደብ ብቻ ተቆፍሮ በሚወጣ ተአምረኛ ቁሳቁስ የምንኖር ቢሆን ነበር፡፡ 

ካልሆነ ግን ወደብ በሚታወቀው የገቢና የወጪ እቃ ማስተላለፊያነቱ ከተመዘነ ኤርትራ በማንኛውም ሚዛን አንገት አደለችም፡፡ ልትሆንም አትችልም፡፡
 
እንዲያውም ከሸቀጥ አንጻር ከታየ አንገት መባል የነበረባት ወደብ አልባዋ ኢትዩጵያ ናት፡፡ ኤርትራ በማታመርታቸው ጥሬ እቃዎች ጥሩ ላኪ አገር ሆና የነበረውም ከጦርነቱ በፊት ይህን ሀብታችንን ከኛ ገዝታ በመውሰድ ታቀርብ የነበረ በመሆኑ  እንደሆነ መረሳት የለበትም፡፡ ጉዳዩ ከህዝቦች መብት አንጻር መታየቱ ከቀረ በሚል ያመጣሁት ንጽጽር እንጂ የሁለቱ ህዝቦች ጉዳይ ከሀብት አንጻር መመዘን አለበት ብዬ አላምንም፡፡
 
ወደቡን ስላጣነው ማጣጣል አለብን ብዬም አላምንም፡፡ ወደብ ራሱን የቻለ አስፈላጊነት እንዳለው አልዘነጋም፡፡ ለወደብ ሲባል ግን ወጣቱ እየታፈሰ ለጦርነት ሲማገድ መክረም አለበት የሚል ደካማ አማራጭም አልወስድም፡፡ ወደብ ዛሬ ባለው ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው ሲመዘን የሚኖረው ተጽእኖ ወደብ ወይም ሞት የሚያሰኝ አደለም፡፡
 
በተለያዩ ግዜያት ወደብ አልባ በሆኑ አስራ ስድስት የአፍሪካና 31 አለማቀፍ ደሀ አገሮች ላይ የተደረገ ጥናት እንደሚያመላክተው ወደብ አልባ አገሮች ወደብ ካላቸው አገሮች ጋር ሲነጻጸር ከትራንስፓርት እና ተያያዥ ወጪዎች አኳያ 50 በመቶ ከፍ ያለ ወጪ ለማውጣት ይዳረጋሉ፡፡

አንዳንድ ጥናቶችም ወደብ አልባ አገሮች ወደብ አልባ በመሆናቸው ብቻ አመታዊ ኢኮኖሚያ እድገታቸወ 0.5 በመቶ ድረስ የእድገት ምጣኔ ቅናሽ እንደሚያሳዩ ይጠቁማሉ፡፡ ይህ ግን በደሀ ወደብ አልባ አገሮች ሁኔታ አኳያ እንጂ ወደብ አልባነት ከዚህ ጋር የግድ የሚያቆራኝ ሆኖ አደለም፡፡

አንደኛ እነዚህ ደሀ ወደብ አልባ ሀገራት በደሀ ባለወደብ ሀገራት አጎራባችነት ያሉ በመሆኑ ያልዳበረ መጓጓዣ እና ትራዚት አገልግሎት ስላላቸው ወደብ አልባውንም አገር ራሳቸውንም በከፍተኛ ደረጃ ተጠቃሚ ማድረግ በሚያስችል ቁመና ላይ የማይገኙ በመሆኑ ነው፡፡  

ወደብ አልባ ሆነው ሲያበቁ የርስ በርሱ ንግድ ልውውጥ በተጠናከረበት እና የትራንስፓርት ዘርፉ ባደገበት አካባቢ ያሉ እንደ ኦስትርያ ስዊዘርላንድ እና ቤልጂየም ያሉ አገሮች ምን ያክል መልማት እና የበለጸጉ ሀገሮች መሆን እንደቻሉ የምንታዘበው ነው፡፡
እነዚህ አገሮች ሸቀጥ ለማስገባት የግድ ወደባህር በር የማያዩበት ከበለጸጉት ጎረቤቶቻቸው የሚገበያዩበት የወጪ ንግዳቸውንም ወደብ በወሳኝነት ሳያስፈልግ ለጎረቤቶቻቸው የሚያቀርቡበት ሁኔታ ስላለ ለኛ ወጥመድ የሆኑ ሁኔታዎች ለነሱ እምብዛም ቁምነገራቸው ያልሆነበት ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ 

የኛ ከባቢያዊ ሁኔታ ከዚህ አኳያ ያለውን በጎ ያልሆነ ተጽእኖ እንገነዘባለን፡፡ ለዚያ ነው ኢህአዴግ ጎረቤቶቻችን እንደ አቅም እንጂ እንደ ጠላት የማይፈርጀው፡፡ የሱማሌ የሱዳንና ሌሎች ከባቢያዊ ሁኔታዎችንና አህጉራዊ ሁኔታዎችን በትኩረት ኢህአዴግ የሚተጋባቸው የአህጉሪቱ ማደግ የኢትዩጵያ ማደግ የከባቢው መለወጥ የኢትዩጵያ ለውጥ መሆኑን በመረዳት ነው፡፡

በመሆኑም ከነዚ መነሻዎች ተነስተን ስንቃኝ ኤርትራ ለኢትዮጵያ አንገት የምትሆንበት ቤሳቢስቲን ተጨባጭ ማስረጃ የለም፡፡ ለኔ ወጣትን ለጦርነት ሲማግዱ ከመኖር የግድ የሚል ከሆነ 0.5 አመታዊ የእድገት ምጣኔያችንን ቀርቶብን በሰላም መኖራችን ሁነኛውም መለኛውም አማራጭ ነው፡፡ ይሄ ማለት ኢትዩጵያና ኤርትራ አንድ ሊሆኑ የሚችሉበት እድል ካለ ባፍጢሙ ይደፋ ማለት አደለም፡፡ ግን የሚሆነው በመግባባት እና በመተማመን ነው፡፡ በአንገትና በበድን የሰከረ አተያይ የሚመራ ፖለቲካ ለዚህ መሰሉ ስክነት የታደለ አደለም፡፡

ኢህአዴግ በለጋ እድሜው ይህን አማራጭ ተረድቶ ማቅረብና ማስተግበሩም በለጋ እድሜው የፈጸመው ሁሌም የሚታወስ በሳል እና ትልቅ አበርክቶው እንደሚሆን አምናለሁ፡፡ ከወንበሬ ብድግ ብዬ ለዚያኔዎቹ ወጣቶች ለአሁኖቹ ጎልማሶች አድናቆቴን እገልጻለኁ፡፡ በርግጥም ኤርትራ አንገት አልነበረችም ዛሬም ወደፊትም አንገታችን አትሆንም፡፡  

አሰብም እንደ ወደብ እንደ ወርቅ እየተቆረጠ የሚሸጥ ጸጋ አደለም፡፡ አገልግሎት ሲሰጥ ብቻ ነው ሀብት የሚሆነው፡፡ አገልግሎት ሊሰጥ የሚችለው ደግሞ ለኛ ብቻ ነው፡፡ እኛ ስንጠቀመው ለኤርትራውያኑ ግዙፍ ገቢ ይሆናል ትንሽ ቁጥር ያለው ህዝብ ከመሆናቸው አንጻር ትልቋ አገር የሚኖራት ትልቅ የወጪና የገቢ ንግድ የሚያስገኘው ዳጎስ ያለ ገቢ ስለሚኖር፡፡ እንዲያውም ኤርትራ በአካባቢው ተመሳሳዩን አገልግሎት ሊያቀርቡ የሚችሉ በርካታ ሀገሮች መኖራቸውን ተረድታ የተሻለ አገልግሎት ለመስጥትና ተመራጭ ወደብ ለመሆን ተፍ ተፍ ማለት ነበረባት፡፡
 
ለአንድ አገር አንገት የሚሆን ሚና ሊሆን የሚችለው የራሱ መንግስት የአመራር ሚናና የህዝቡ ተነሳሽነት ብቻ ነው፡፡ በመሆኑም ነው የአንገትነት ታፔላ የተለጠፈላት ሀገርም ከሄደች በኋላ እቺ አገር በአለም አቀፍ ደረጃ ፈጣን እድገት ከሚያስመዘግቡት ቻይናና ሕንድ ተርታ መግባት የቻለችው፡፡ አንገታችን ወዴት ነሽ ብሎ መጠየቅ ተገቢ ነው፡፡ 

አንገታችን ልማታዊ ስራዎቻችን ላይ ያነጣጠረ ትጉህ መንግስት ትጉህ ፓርቲና ትጉህ ህዝብ እንጂ ኖረንም ቀረም ወደብ አደለም፡፡ ወደብ ቢኖረው እሚጠላ የለም ኖረም ቀረም ግን የህዝቡን እና የመሪ ድርጅቶችን አይተኬ ሚና ለወደብ በመስጠት ራሳችንን አሳንሰን ልናይ አንችልም፡፡ ብናደርገውም ስህተት ከመሆን ያለፈ ፋይዳ የለውም፡፡

ኤርትራ በኤርትራውያን ውሳኔ አንድ ሆና ብትኖር የሚጠላ ያለ አይመሰለኝም፡፡ ቢሆን ደስተኛ ከሚሆኑት መካከል ኢህአዴግ አንዱ አንደሚሆን አምናለሁ፡፡ አንገት በሚል መንፈስ ግን አደለም፡፡ አንድ ሆኖ ለረጅም ግዜ እንደኖረ ህዝብና አብሮ መኖሩ ለሁለቱም ህዝቦች የሚያስገኘው ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጥንካሬ ስለሚኖረው ነው፡፡

ሁኔታ እንዳይፈጠር የተበላሸ ሚና የነበረው ደግሞ ዛሬም ትላንትም ኤርትራን እንደ አንገት የሚያየው የተቃውሞ ቡድን ነው፡፡ በዚህ በሰከረ ተመሳሳይ ስሌት ሲነዳ የነበረው ሻብያ ወደቡ የግመል ማጠጫ ከመሆን በዘለለ ፋይዳ እንደሌለው በተግባር ሲረዳ ደግሞ የገባበት አዘቅት አካባቢውን በማተራመስ ኢትዮጵያን የኤርትራ ብቻ ደምበኛ አድርጎ የማቆየት አዝማሚያ ነው፡፡ በሶማሌ ያሰገባው እጅ ከጂቡቲ ጋር በድንበር ስም ሊፈጥረው የሞከረው ቀውስ በሱዳን በኩል ሊፈጥር የሚሞክረው ቀውስ ተዳምረው ሲታዩ  እውነታውን ትቶ ራሱን እንደ አንገት ሲቆጥር የነበረው ሻብያ ከገጠመው ራሱን አልቆ የማየት ውርደት ለመውጣት የሚደርገውን መፍጨርጨር ነው፡፡  

ኤርትራ የሆነችውን እንጂ ያልሆነችውን ሆና በመታየት በኢትዮጵያ ላይ ልታደርስ የምትችለው ተጽእኖ አይኖርም፡፡ በመሆኑም ኤርትራ አንገት አደለችም ብቻ ሳይሆን ይሄ የወደብ አገልግሎት አቅርቦት ስራዋም በርካታ ተፎካካሪዎች ያሉበት በመሆኑ የተሻለ አገልግሎት በማቅረብ ከፍ ያለ ገቢ ለማግኘተ ቀና ደፋ የሚጠብቃት ሀገር ጭምር ናት ማለት ነው፡፡ በየትኛውም መስፈርት አካባቢውን በማመስ ኢትዮጵያን ለማተራመስ የምትሰራውም ስራ ኢትዮጵያ ልትቆጣጠረው እማትችለው አይሆንም፡፡
 
በመሆኑም አንገት ተብላ የምትቀርበው ኤርትራም አንገት አደለችም ኤርትራን አንደ አንገት የሚያቀርቡልንም ያለኛ ለአገርና አንድነት አሳቢ የለም የሚሉንም ፖለቲከኞችም ለራሳቸው ከሚሰጡት ግምት በተቃራኒ የአገራችንን ፖለቲካና መፍትሄዎቹን በቅጡ ያልተገነዘቡ ናቸው፡፡ አገሪቱ የገጠሟትን ችግሮች በውል ያልተረዱ በመሆኑም መሰረታዊ ለውጥ ሊያመጣ የሚችል ፖለቲካዊ መፍትሄም ሊያቀርቡ የማይችሉ ሀይሎች ሀገሬ ሀገሬ ስላሉ ብቻ ራሳቸውን ጥሩ ፖለቲከኛ አድርገው ያዩበት እንደሆነ ከዚህ መረዳት ይቻላል፡፡

ይህም መሰሉን የተሳሳተ ግንዛቤያቸውን ባለፉት 20 አመታት በላይ ሊያርሙት ያልቻሉ መሆኑ ደግሞ ከስህተታቸው ለመማር ይቅርና የለም ተሳስተናል ለማለት ያላቸውን ደካማ ስነምግባር የሚያሳይ ነው፡፡ በዚህ ቁመና ሀገር የመምራት ሀላፊነት መረከብ ቀርቶ ለመረከብ ማሰብ በራሱ የሀገሪቱን ህዝቦች ህሊናዊ ብቃትና የምዘና አቅም መናቅ ይመስለኛል፡፡

ወደብን ወሳኝ ጉዳይ አይደለም ብሎ ስለተረዳ ብቻ ሳይሆን ለህዝቦች ውሳኔና ፖለቲካዊ ጥያቄ አክብሮት ስላለው የህዝቦችን ራስ የማስተዳደር እስከ መገንጠል ህገመንግስታዊ ድንጋጌ ያሰጠው ፓርቲ ከዚያ ለጥቆ የጠሩ ፖሊሲዎች በመቅረጽ ሀገር ወደማልማት ስራዎቹ ፊቱን አዙሯል፡፡ በዚያም በቃል ያብራራውን በተግባር አሳክቶ በማሳየት ባለወደቧ ሀገር ያላሳካችውን ወይም ያላሳኩትን የእድገት ምጣኔ ባለፉት አስርት አመታት ደጋግሞ ሀገራችን እንድታሳካ በሳል አመራር በመስጠት ድርብርብ ድል አጣጥሟል፡፡

በመሆኑም የወደብን ሚዛን በአግባቡ ያሰላ ወደብ ያላቸው ዙርያውን ያሉ የአፍሪካ ሀገሮች ያላሳኩትን ባለሁለት አሀዝ እድገት ላለፉት 9 አመታት በተከታታይ ያሳካ ፓርቲና በዚሁ ፓርቲ ዙርያ መተማመን የፈጠረ ሕዝብ የገነባን መሆኑ አኩሪ ሂደት ነው፡፡ ይህን ማሳካት የተቻለው ደግሞ ሁሉም ነገር ወደ ወደብ ወደ ጦርነት ግንባር የሚለው መፈክር በሁሉም ነገር ድህነትንና ኋላቀርነትን ወደ መናድ ግንባር በሚል ቅኝት በመተካቱ ነው፡፡