Tuesday, October 8, 2013

#‎አማራጭ‬ ፓርቲ #አማራጭ ፕሮግራም ነው



የፖለቲካ ፓርቲ ብዝሀነት አብይ አላማ ለአንድ ሀገር ህዝቦች የተለያዩ የፖለቲካ አማራጮችን ማቅረብ ነው፡፡ የተቃውሞ ፖለቲካ ከገዢ ፓርቲ አንጻርም ከተመዘነ ሌላ አጀንዳ ሊኖረው አይችልም:: ገዢ ፓርቲው እያስገኘ ካለው ስኬት የተሻሉ ስኬቶች ማስመዝገብ የሚችሉ የፖሊሲ አማራጮች የፖሊሲ አማራጩ እምብዛም ልዩነት ከሌለው ደግሞ የተሻለ የመፈጸም አቅም እና ስነምግባር ያለው ፓርቲና አባላት በማደራጀት ህዝቡ ይህን በመሰለው ፓርቲ አማራጭ የማስፈጸም አቅም ዙርያ መተማመን እንዲፈጥር ማድረግ ነው፡፡

ይህን በመሰለ አማራጭም ሰከን ብሎ ገዢ ፓርቲን መርታት በሂደትም ጠንካራ ዴሞክራሲያዊ ፖለቲካዊ ስርአት መመስረት ይቻላል፡፡ ይህን መሰሉን ጠንካራ ፖለቲካዊ ስርአት ለማቋቋም ደግሞ ቀስ በቀስ ጠንካራ ዴሞክራሲያዊ እሴቶችን መፍጠር ተገቢ ነው፡፡

ያን የመሰሉ እሴቶች የሚኖሩን ሰከን ያሉ አማራጮች በማቅረብ የተጠመዱ ፓርቲዎችና መልእክቶቻቸው እኒህን አማራጮች በማስተዋወቅ ዙርያ ያጠነጠኑ ፓርቲዎችን መገንባት የቻልን እንደሆነ ነው፡፡ በወሳኝነት ይህን የመሰለ ቁመና የሚኖራቸው ፓርቲዎች አብይ ስራ ውስጣዊ ቁመናቸውን ማነጽ የጠሩ ፕሮግራሞችን መንደፍ በነደፏቸው ፕሮግራሞች ዙርያ መልእክቶች ማበጀት እነዚሁኑ መልእክቶች በትጋት በማሻሻጥ ላይ ያተኮሩ ይሆናሉ፡፡

ያኔ ነው በሂደት በህዝቡ እምነት እየተቸራቸው አማራጮቻቸው መወያያ እየሆኑ የአባሎቻቸው ቁመና ከሌሎች አባሎቸ ቁመና አኳያ እየተመዘነ በእንድ በኩል የዳበሩ ብቁ ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉበት የተለያዩ አቋሞች የሚራመዱበት ዴሞክራሲያዊ እሴቶቹ የጎለበቱበት የፖለቲካ ብዝሀነት በሌላ ጎኑ ደግሞ ይህን በመሰለው ሂደት አቀጣጣይነት የዳበረ የማገልገል መንፈስ አፈጻጸም እና ልማት የሚስተዋልበት መንግስታዊ እና ድርጅታዊ መዋቅሮች እየተገነቡ የሚሄዱበት ሁኔታ ይፈጥራል፡፡

አሁን ያለውን ሁኔታ ስናጤን ግን ከስልሳ እስከ 90 የሚደርሱ ፓርቲዎች እናስተውላለን፡፡ ይሄ ግን ተመሳሳይ ቁጥር ባለው አማራጭ የተተረጎመ አደለም፡፡ ከአማራጮች ይልቅ የፓርቲዎቹ ቁጥር የሚያመላክተው በተለያዩ ቡድኖች የተሰባሰቡ ግለሰቦችን በፖለቲካ ስም የመነገድ ጥቅሞች የማጋበስ ፍላጎት ነው፡፡ ስንኩዋንስና ዘጠና በኛ የፖለቲካ መድረክ የለየላቸው ጥርት ባሉ ፖለቲካዊ አይዲዮሎጂና ፍልስፍና የሚመሩ 2 ወይም 3 አማራጮች አናይም፡፡

እየተዘጋጀ ካለ መጽሀፍ የተቀነጨበ

No comments:

Post a Comment